የኡጋንዳው ካምፓላ ኩዊንስ አሰልጣኝ የሆነው ፍሬው ኃይለ ገብርኤል የኡጋንዳ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የታህሳስ ወር ኮከብ አሰልጣኝ በመሆን ተመርጧል።
የቀድሞው የሉሲዎቹ አሰልጣኝ በወሩ ቡድኑን እየመራ ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች በሶስቱ ሲያሸንፍ በአንዱ ነጥብ ተጋርቷል።
ቡድኑ በታህሳስ ወር ላይ ቱሮ ኩዊንስን 2 – 1 ፤ ኦሊላ ኤች ኤስን 3 – 0 ፣ ካዌምፔ ሙስሊም ሌዲስን 4 – 1 ሲረታ ከሺ ማሩንስ 0 – 0 ተለያይቷል።
አሰልጣኝ ፍሬው የወሩ ኮከብ ሆኖ መመረጡን ተከትሎም የ500 ሺህ የኡጋንዳ ሽልንግ እና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል።
- ማሰታውቂያ -
በአሰልጣኝ ፍሬው ኃይለገብርኤል የሚመራው ካምፓላ ኩዊንስ በሊጉ ካዳረጋቸው 11 ጨዋታዎች በ7 አሸንፎ በ4 አቻ በመለያየት በ25 ነጥቦች ሊጉን በመምራት ላይ ይገኛል።


