የኢትዮጵያ ቡና እና የዋልያዎቹ የፊት መስመር አጥቂ በዘንድሮው የውድድር ዓመት ደምቆ ሲታይ በ በርካታ የአፍሪካ ክለቦች አይን ውስጥ ማረፍ ችሏል ።
በተለይም በዘንድሮው የውድድር ዓመት የሊጉን ከፍተኛ ግብ አግቢነት ሪከርድ ይሰብራል ተብሎ ሲጠበቅ በዛሬው ዕለት የእውቅና ሽልማት እንደተበረከተለት ለማወቅ ተችሏል ።
አቡበከር ናስር በዛሬው ዕለት በ ቡናማዎቹ የቀድሞው ተጫዋች ሙሉአለም ጥላሁን የመጫወቻ ቁሳቁሶች በስጦታ መልክ እንደተሰጠው ታውቋል ።

የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋች ሙሉአለም ጥላሁን በአሁን ሰዓት ኑሮውን በሀገረ ጀርመን አድርጎ ሲገኝ ሽልማቱን በእህቱ ፀጋ ጥላሁን በኩል ቦሌ ብርሀኔ አደሬ ሞል በሚገኘው ሱቁ ለአቡበከር ናስር ማበርከት ችለዋል ።
አስተያየት ይስጡ