በ2014 የዉድድር አመት ይበልጥ ተጠናክረው ለመቅረብ እንዲረዳቸዉ በዝዉዉሩ ላይ ተጫዋቾችን በማስፈረም ላይ የሚገኙት ኢትዮጵያ ቡናዎ አዲስ የተከላካይ መስመር ተጫዋች ወደ ቡድናቸው ቀላቅለዋል።
በዛሬው ዕለት ለክለቡ ፊርማዉን ያኖረዉ የተከላካይ ስፍራ ተጫዋቹ ነስረዲን ኃይሉ ሲሆን በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ከመከላከያ ጋረ ከተለያየ በኋላ ወደ ኢትዮ ኤሌክትሪክ አምርቶ አመቱን ካሳለፈ በኃላ በመጨረሻም ለመዲናዉ ክለብ ኢትዮጵያ ቡና ለመጫወት የሶስት አመት ዉል ፈርሟል።
ተጨዋቹ በቀጣይ ዓመት አሰልጣኝ ካሣዬ አራጌ የተከላካይ ክፍሉን ለማጠናከር ለሚያደርገው እንቅስቃሴ ጉልህ ሚና ይኖረዋል ተብሎም ይጠበቃል።


