የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎቹን መቻልን 1 – 0 በመርታት ያጠናቀቀው ኢትዮጵያ ቡና የውድድር ዘመኑ አጋማሽ የምርጥ ተጫዋች ዕጩዎቹን ይፋ አድርጓል።
በዕጩዎቹ ዝርዝር የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ እና የጥቅምት ወር የክለቡ የወሩ ምርጥ ተጫዋች አንተነህ ተፈራ እና የህዳር ወር የክለቡ የወሩ ኮከብ ተብሎ የተመረጠው ናይጄሪያዊው ዲቫይን ዋቹኩዋ መካተት ችለዋል።
ሁሉንም የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች(17) ያደረገው እና በዘጠኝ ጨዋታዎች ግብ ያላስተናገደው ግብ ጠባቂው ዳንላንድ ኢብራሂም ፤ የቡድኑ አምበል ራምኬል ጀምሰ ፤ የቀኝ መስመር ተከላካዩ ረጂብ ሚፍታህ እና የመሀል ተከላካዩ ወልደአማኑኤል ጌቱ በዕጩዎቹ ዝርዝር የተካተቱ ሌሎች ተጫዋቾች ናቸው።
የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች የውድድር ዘመኑ አጋማሽ ምርጥ ተጫዋቻቸውን በክለቡ ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ ላይ መምረጥ እንደሚችሉ ተገልጿል።
- ማሰታውቂያ -



