ኢትዮጵያ ቡና ናይጄሪያዊውን የመስመር አጥቂ አዳሙ አቡበከርን በሁለት ዓመታት ውል ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።
ተጫዋቹ ያለፈውን የውድድር ዘመን በፕላቲዩ ዩናይትድ ያሳለፈ ሲሆን በሊጉ ባደረጋቸው 30 ጨዋታዎች 6 ግቦችን አስቆጥሮ 5 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል።
የእግር ኳስ ህይወቱን በኖርዌይ በሚገኝ አካዳሚ የጀመረው የ28 ዓመቱ ተጫዋች ፕላቲዩ ዩናይትድን ጨምሮ ለአራት የናይጄሪያ ክለቦች ተጫውቶ አሳልፏል።
በ2022/23 የውድድር ዘመንም ከኢንዬምባ ክለብ ጋር የናይጄሪያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሆኗል።
- ማሰታውቂያ -
ኢትዮጵያ ቡና ከጥቂት ቀናት በፊትም ዘላለም አባተን ከወላይታ ድቻ ማስፈረሙ የሚታወስ ነው።



