የመስመር አጥቂው ሸምሰዲን መሐመድ ኢትዮጵያ ቡና አመራ።
ከአራት አመት በፊት ከፋሲል ከነማ ወጣት ቡድን ከተገኘ በኋላ ላለፉት አመታት በፋሲል ከነማ መለያ በተለይ በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን ጥሩ ጊዜን ያሳለፈው የመስመር ተጫዋቹ ሸምሰዲን መሐመድ ከልጅነት ክለቡ ፋሲል ከነማ ጋር በመለያየት ከሰሞኑ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ልምምድ እየሰራ የነበረ ሲሆን በልምምድ ሜዳ ላይ ጥሩ ጊዜን በማሳለፉ የመዲናይቱን ክለብ ተቀላቀለ።
ተጫዋቹ በአጋማሹ የቡናማዎቹ ሦስተኛው ፈራሚ ሆኗል።



