በዛሬው ዕለት ኢትዮጵያ ቡናን ከምስረታው አንስቶ በተለያዩ ሀላፊነት ከአርባ አመት በላይ መርተው ከፕሬዝዳንትነት የለቀቁት መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ ምን አሉ ?
“ኢትዮጵያ ቡና ትልቅ ክለብ ነው። ለዚህ ክለብ ብዙ ነገር ሆነው ያለፉ ብዙ ሰዎች አሉ ፤ እነሱን እያሰብኩ ስፅፍ ፣ ሳወጣና ሳወርድ ነበር። ዛሬ ቦታዬን የምለቀው ደስተኛ ሆኜ ነው። ምክንያቱም ክለቡ ወደ አስተማማኝ እጅ ነው የተሸጋገረው። አሁን ትልቁ ነገር ክለቡ መልካም ሰዎች እጅ መውደቁና ቀጣይነቱ መረጋገጡ ነው። ኢትዮጵያ ቡና አይፈርስም።
“ሌላው ነገር ብዙ ያስቀየምኳቸው ሰዎች አሉ ፤ እነሱን ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ። ስናገር ፣ አንዳንድ ውሳኔዎችን ስወስን ፣ ሀሳብ ይዘው የሚመጡ ሰዎችን ያለመስማት ፣ ያለማባበልና ቁጭ አድርጎ ያለማወያየት ችግር ነበረብኝ። ዕድሉን አልሰጣቸውም ነበር። ለዚህ ከልቤ ይቅርታ እጠይቃችኋለሁ። ደጋፊዎቻችንንም ይቅርታ እጠይቃለሁ።
የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ሁልጊዜም ውጤትን ይፈልጋሉ። አንዳንድ ጊዜ የሚፅፉትና የሚናገሩት ከውጤት ማጣት የተነሳ እንደሆነ ይገባኛል። ነገር ግን ሁሉም ሰው ይሄንን ይሸከማል ማለት አይቻልም። አንዳንድ ሰው ቆዳው ስስ ነው ፤ ቶሎ ሊከፋ ይችላል። ስለዚህ ከመፃፍና ከመናገር በፊት ትንሽ ማስተዋል ቢኖር መልካም ነው እላለሁ። ይህ ትልቅ ክለብ ነው ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው።
አስተያየት ይስጡ