ቡናማዎቹ ከኢትዮጵያ መድን ጋር የተለያየውን አማካይ የግላቸው አደረጉ።
እግር ኳስን በክልል ክለቦች ሻምፒዮና ትውልድ ሀገሩን ቤንሻንጉልን ወክሎ ሲጫወት ከሁለት አመት በፊት አዳማ ከተማን ሲያሰለጥኑ በነበሩት አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ ዐይን ውስጥ ገብቶ ክለቡን በመቀላቀል ሁለት የውድድር ዘመናትን በክለቡ ካሳለፈ በኋላ በያዝነው የውድድር ዘመን ለኢትዮጵያ መድን በመፈረም ቆይታን ማድረግ ችሏል።
በአሰልጣኝ ገብረመድኅን ሐይሌ የልቀቅ ጥያቄን ያስተናገደው አማካዩ ሙሴ ኪሮስ ቀሪ የስድስት ወር ኮንትራት እየቀረው መድንን ለቆ በይፋ ለአንድ አመት ኢትዮጵያ ቡናን ተቀላቅሏል።


