በደጋፊው ዘንድ ተደጋጋሚ ቅሬታን እያስተናገዱ የሚገኙት የኢትዮጵያ ቡና አሰልጣኝ እና ተጫዋቾች ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው።
ኢትዮጵያ ቡናን ከተስፋ ቡድኑ አንስቶ በማሰልጠን ከክለቡ ጋር መተዋወቅ የቻለው ወጣቱ አሰልጣኝ አብይ ካሳሁን በ2017 የውድድር ዘመን ደግሞ የአሰልጣኝ ነፃነት ክብሬ ረዳት በመሆን በዓመቱ አጋማሽ ላይ ተሹሞ ክለቡን ሲያገለግል መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን በያዝነው የውድድር ዘመን ቡድኑን በዋና አሰልጣኝነት በመረከብ በፕሪምየር ሊጉ ቆይታን እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ቡድኑም ካደረጋቸው አስር የሊግ መርሀግብር ማግኘት ከነበረበት ሰላሳ ነጥብ አራት ተሸንፎ ፣ ሦስት አሸንፎ ፣ በሦስቱ አቻ ወጥቶ አስራ ሁለት ብቻ ይዞ በደረጃ ሰንጠረዡ 13ኛ ላይ መቀመጥ የቻለ ሲሆን ክለቡም በተደጋጋሚ በደጋፊው ተቃውሞን እያስተናገደ ለሚገኘው ወጣቱ አሰልጣኝ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤን የሰጠ ሲሆን ከቀጣይ ሁለት ጨዋታዎች ክለቡ በተከታታይ ድሎችን የማያገኝ ከሆነ ለማሰናበት እንደሚገደድ ተሰምቷል።
ከአሰልጣኝ አብይ በተጨማሪ ጋናዊው ግብ ጠባቂ ዳላንድ ኢብራሂም ፣ ናይጄሪያዊው አማካይ ዲቫይን ዋቹኩዋ ፣ ዩጋንዳዊው አጥቂ ሻባን መሐመድ ፣ ከከፍተኛ ሊጉ ሶዶ ከተማ የፈረመው ግብ ጠባቂው እንዳሻው እሸቴ ፣ የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ አማካይ አላዛር ሳሙኤል ፣ ከአዳማ ከተማ የፈረመው አማካዩ ፉዓድ ኢብራሂም ፣ የተስፋ ቡድኑ ፍሬ የሆነው አጥቂው አማኑኤል አድማሱ እና ሌላኛው አጥቂ በረከት ብርሀኑ ከአቅም በታች በሆነ እንቅስቃሴ ክለቡን እየጎዳችሁ ነው በሚል ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ስምንት ተጫዋቾች ሆነዋል።
ክለቡ በተሰናባቹ ስራ እስኪመጣ ገዛኸኝ ወልዴ ምትክ አዲስ ስራ አስኪያጅ ለመሾም በይፋ የስራ አስኪያጅ ቅጥር ማስታወቂያን ማውጣቱም ይታወሳል።


