የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የፋይናንስ ተቆጣጣሪ ኮሚቴ ከደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ውጪ ተጨማሪ ገንዘብ የተገኘባቸው ተጨዋቾች ማስረጃ እንዲያቀርቡ ጠየቀ።
በ2017 ዓ.ም ውል ያላቸው የቡድን አባላት የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች እንዲመረምር በተወሰነው መሰረት ከውል ስምምነታቸው (ደሞዝና ጥቅማጥቅም) ውጪ ተጨማሪ ገንዘብ የተገኘባቸው 43 ተጫዋቾች በተጠረጠሩበት ላይ ማስረጃ እንዲያቀርቡ ተቆጣጣሪ ኮሚቴው ጠይቋል።
በተጨማሪም ውል ባላቸው ቀሪ ቡድን አባላቶች ላይም ምርመራው
እየተደረገ እንደሚገኝ የፋይናንስ ተቆጣጣሪ ኮሚቴው አስታውቋል።



