የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር በሊጉ የቀጥታ ስርጭት መብት ዙሪያ ምንም አይነት ጨረታ አለማውጣቱን አስታወቀ።
አሚኮ በሊጉ የቀጥታ ስርጭት መብት ጉዳይ ዙሪያ ላቀረበው ቅሬታ የአክሲዮን ማህበሩ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሰይፈ በሰጡት ምላሽ በቀጥታ ስርጭቱ ዙሪያ ምንም ያወጣነው ጨረታ የለም ነገር ግን ከዲ ኤስ ቲቪ ጋር የነበረን ውል መጠናቀቁ ከታወቀ በኋላ አምስቱ ጣቢያዎች እኛ እንችላለን ብለው በመጠየቃቸው የውድድሩን ሰነድ ሰጥተናቸው እስከነገ ድረስ ምላሻቸውን እየጠበቅን እንገኛለን” ሲሉ መልሰዋል።
አቶ ክፍሌ ከአሚኮ ከፍተኛ አመራር መሃል ነኝ ያለ ግለሰብ ደውሎ ጨረታውን ላክልኝ ብሎ ልኬለታለሁ ቀነ ገደቡ ነገ ነው ስለው ግዴለም እንደርሳለን ካለኝና ሰነዱን ከወሰደ በኋላ ጉዳዩን ወደሚዲያ መውሰዱ አላማው አልገባኘም ሲሉ ተናጎረዋል።

- ማሰታውቂያ -
ዋና ስራ አስኪያጁ እንደገለጹት ያወጣነው ጨረታ በሌለበት የቴሌቭዥን ጣቢያዎቹ ራሳቸው መጥተው ለእኛ ስጡን ባሉበት ሂደት የአሚኮ ቅሬታ ተገቢነት የለዌም አሚኮ ምን እንዳለው አናውቅም አቅም እስካላቸው ድረስ የምንለየው ሚዲያ የለም መነጋገር እየቻልን ቅሬታውን ለሚዲያ ፍጆታ ማዋል መፍትሄ አያመጣም ” ሲሉ ያለውን ሂደት አብራርተዋል።
አሚኮ ያለ ግልጽ ጨረታ ሚዲያዎች ሰነዱን የወሰዱበትና የተመረጡበት መንገድ ተገቢ አይደለም በሚል ዛሬ ከቀትር በኋላ ለአክሲዮን ማህበሩ ቅሬታ አዘል ደብዳቤ ማስገባቱ ታውቋል።


