የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ፣ ምርጥ ግብ ጠባቂ እና ምርጥ ተስፈኛ ተጫዋች ዕጩዎች ይፋ ሆነዋል።
በኮከብ ተጫዋች ዘርፍ ሻምፒዮኑ ኢትዮጵያ መድን ሶስት ተጫዋቾችን አስመርጧል።
ሀይደር ሸረፋ ፣ ዳዊት ተፈራ እና መሐመድ አበራ በዕጩ ዝርዝሩ የተካተቱ የኢትዮጵያ መድን ተጫዋቾች ናቸው።
ኢትዮጵያ ቡና ደግሞ ሁለት ተጫዋቾችን ሲያስመርጥ ራምኬል ጀምስ እና ዲቫይን ዋቹኩዋ ተካተዋል።
- ማሰታውቂያ -
የሀዋሳ ከተማው አሊ ሱሌማን እና የመቻሉ ሽመልስ በቀለ በዕጩ ዝርዝሩ መካተት የቻሉ ተጫዋቾች ናቸው።
በምርጥ ግብ ጠባቂ ዘርፍ ደግሞ የኢትዮጵያ መድኑ አቡበከር ኑራ ፣ የኢትዮጵያ ቡናው ዳንላድ ኢብራሂም እና የባህርዳር ከተማው ፔፔ ሰይዶ ተካተዋል።
በዓመቱ ምርጥ ተስፈኛ ተጫዋች ዘርፍ ስድስት ተጫዋቾች በዕጩነት ሲቀርቡ የኢትዮጵያ መድኑ በረከት ካሌብ ፣ የኢትዮጵያ ቡናው ይታገሱ እንዳለ ፣ የቅዱስ ጊዮርጊሱ ሔኖክ ዮሐንስ ፣ የባህርዳር ከተማው ሔኖክ ይበልጣል እና የመቀሌ 70 እንደርታው ዘረሰናይ ብርሀኑ ተመርጠዋል።
የሊጉ ተከታታዮች እስከ ሰኔ 13 ድረስ ድምፅ መስጠት እንደሚችሉ ተገልጿል።


