1. ሸሪፍ መሀመድ(መቐለ 70 እንደርታ) ሐሙስ ጥቅምት 14 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከድሬደዋ ከተማ ጋር ባደረገው የ5ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 88 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
2. መቐለ 70 እንደርታ ክለቡ ከ ከድሬደዋ ከተማ ጋር ባደረገው የ5ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ የክለቡ ተጠባባቂ ተጫዋቾች በተቀመጡበት የምክር መስጫ ቦታ ላይ ከሚገኙት መቀመጫዎች መካከል የአንዱ የእጅ መደገፊያ ስለመሰበሩ ሪፖርት ተደርጓል። ስለሆነም ክለቡ የተሰበረውን የእጅ መደገፊያ እንዲያሰራ ወይም የስታድየሙ ባለቤት አሰርቶ የሚያቀርበውን ዋጋ እንዲከፍል ወስኗል፡፡


