By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: “በ2017 የውድድር ዘመን ሻምፒዮን እና ወራጅ ክለቦች መኖር የለባቸውም በሚል አንዳንድ ክለቦች ጠይቀዋል።” “በ25 ተጫዋቾች ላይ ማጣራት እያደረግን ነው።” መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ ፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክስዮን ማህበር ቦርድ ሰብሳቢ
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“በ2017 የውድድር ዘመን ሻምፒዮን እና ወራጅ ክለቦች መኖር የለባቸውም በሚል አንዳንድ ክለቦች ጠይቀዋል።” “በ25 ተጫዋቾች ላይ ማጣራት እያደረግን ነው።” መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ ፦ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክስዮን ማህበር ቦርድ ሰብሳቢ

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክስዮን ማህበር ባሳለፍነው ቅዳሜ ያካሄደውን 6ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አስመልክቶ በዛሬው መግለጫ ሰጥቷል።

በሊግ አክስዮን ማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ እና ስራ አስኪያጁ አቶ ክፍሌ ሰይፈ ጋዜጣዊ መግለጫውን በጋራ ሰጥተዋል።

በጉባኤው ላይ ተለይተው ሰባት አጀንዳዎች የተነሱ ሲሆን በነሱ ላይ ሰፊ ውይይት መደረጉ ተግልጿል።

አክስዮን ማህበሩ በ2016 ዓመተ ምህረት ከ265,552,342.50 ሚልዮን ብር በላይ ገቢ ማስገባቱን በመጥቀስ ለክለቦች 195,533,491.87 ማከፋፈሉ ተመላክቷል።

- ማሰታውቂያ -

በተጨማሪም ለመንግስት ከ34 ሚልየን ብር በላይ ግብር በመክፈል በሀገሪቱ ከሚገኙ 500 በላይ ተቋማት ጋር ምስጉን ግብር ከፋይ ተቋም በሚል መሸለማቸውን አንስተዋል።

በጉባኤው ከተነሱ ጉዳዮች መካከል የክለቦች የፋይናንስ ስርዓት አንዱ መሆኑም ተጠቅሷል። ይህንን አስመልክቶም የተወሰኑ ክለቦች የውድድር ዘመኑ ሻምፒዮን እና ወራጅ ቡድን መኖር የለባቸውይ በሚል መጠየቃቸውን መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ ገልፀዋል።

ለዚህም ክለቦቹ እንደ ምክንያት ያነሱት እኛ ደንቡን አክብረን እየሰራን በመሆኑ እና ሌሎች ክለቦች ደግሞ ያንን አልተገበሩም በዚህም ተጎድተናል በሚል መሆኑ ተጠቅሷል።

የቦርድ ሰብሳቢው እንዳሉት ከሆነም አንዳንድ ክለቦች የመረጃ አሰጣጥ ላይ ክፍተት ነበረብን በሚል ተጫዋቾችን ያስፈረሙበት የገንዘብ መጠን ሁኔታን አንስተዋል።

ምንም እንኳን ደንቡ ሲወጣ በርካታ ክለቦች በደስታ ተቀብለው ለመተግበር ዝግጁ መሆናቸውን ቢናገሩም የአምናው ውድድር በተጠናቀቀ ማግስት ሶስት እና አራት ደንቡን መጣስ የጀመሩ ክለቦች ነበሩ ብለዋል።

በዚህም የክለቦችን ኃላፊዎቹ ጠርተን አናግረን ማስጠንቀቂያ ሰጥተናል ነገር ግን ደንቡን ከመጣስ ወደ ኋላ አላሉም ሲሉ ተናግረዋል። ደንቡን የጣሱት የክለብ አመራሮች ለክለባቸው ሳይሆን ለግል ኪሳቸው በማሰብ ያደረጉት ነውም ብለዋል።

ይህንን ጉዳይ ለማጣራት ከፌዴራል ፖሊስ እና ከፀረ ሙስና ኮሚሽን ጭምር ተወካዮች ያሉበት ኮሚቴ ተቋቁሞ ማስረጃዎችን በማሰባሰብ ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በዚህም በተጫዋቾች ደረጃ 25 የሚደርሱ ተጫዋቾች ላይ ማጣራት በመደረግ ላይ መሆኑን ያነሱት መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ በተጫዋቾችም ሆነ በክለቦች ላይ ህጋዊ መስመሩን ተከትለን ቅጣት እናስተላልፋለን ፤ የስልክ ቅጂ ማስረጃዎች ሁሉ አሉን ደንቡን ጥሶ ከጥፋት የሚያመልጥ አይኖርም በሚል በእርግጠኝነት ተናግረዋል።

ከክፍያ ጋር በተያያዘ የበርካታ ክለቦች አሰልጣኞች እና አመራሮች የተጨመላለቀ አሰራር ውስጥ ናቸው ብለዋል። በጉዳዩ ላይ ምሳሌ በመጥቀስ ጭምር ያነሱት መቶ አለቃ ፈቀዳ ማሞ ከአንድ ተጫዋች በአመት እስከ አራት መቶ ሺህ ብር ድረስ ኮሚሽን የሚቀበሉ ስለመኖራቸው ጠቅሰዋል።

ከስታድየም ጋር በተያያዘ በአሁን ሰዓት ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነው ስታድየም የድሬዳዋ ስታድየም ብቻ መሆኑ የጠቀሱም ሲሆን ሊጉን ወደ አዲስ አበባ ለመመለስ ንግግሮች በመደረግ ላይ ናቸው ብለዋል።

በተለይም ባሳለፍነው ዓመት የኢትዮጵያ ዋንጫ እና የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የአሸናፊዎች አሸናፊ የፍፃሜ ጨዋታዎች ላይ በተፈጠሩት ከስፖርታዊ መርህ ያፈነገጡ ተግባራት ምክንያት በአዲስ አበባ ላይ የእግርኳስ ጨዋታ ማድረግ ከባድ ነው በማለት የከተማ መስተዳድሩ ውሳኔ አሳልፏሉ ሲሉ ተናግረዋል።።

የቦርድ ሰብሳቢው አክለውም አስቀድሞ እነዚህ ሁኔታዎች ከመፈጠራቸው በፊት ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር በስታድየሙ አጠቃቀም ከስምምነት ተደርሶ ነበር ብለዋል። አሁን ላይ ግን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ወድድሩን በምን መልኩ ወደ መዲናዋ መመለስ ይቻላል በሚለው ላይ ንግግሮችን በማድረግ ላይ እንገኛለን ሲሉ ተናግረዋል።

ከቀጥታ ስርጭት መብት ጋር በተያያዘ በዚህ ዓመት መጨረሻ ውሉ የሚጠናቀቀው ሱፐርስፖርት በዓመቱ 72 ጨዋታዎችን ብቻ አስተላልፋለሁ ማለቱን በመግለፅ ቀሪ ጨዋታቸውን ከፌስቡክ የቀጥታ ስርጭት በተሻገር ለማስተላለፍ በሚያስችል ሁኔታ ላይ ከሱፐርስፖርት ጋር በመነጋገር ላይ ስለመሆናቸው ጠቅሰዋል።

በያዝነው የ2017 ዓመት አክስዮን ማህበሩ በዋነኝነት በቀጣይነት የሊጉ የስያሜ እና የብሮድካስት መብት ሽያጭ ላይ በትኩረት የሚሰራበት ዋነኛ ተግባሩ መሆኑ በመግለጫው ተገልጿል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article አሰልጣኝ ደረጄ ተስፋዬ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር መለያየቱ ይፋ ሆነ…..
Next Article አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ይቅርታ ጠየቀ…..

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችፋሲል ከተማ

ፋሲል ከነማ የተጫዋቹን ውል አራዘመ !

kidus Yoftahe By kidus Yoftahe 6 years ago
Surafel Dagnachew wins best player of the year award
ድሬዳዋ ከተማ ጋናውያን ተጫዋች አስፈርሟል።
የጨዋታ ዘገባ | አዳማ ከተማ በሁለተኛው አጋማሽ ባስቆጠራቸው ግቦች ሶስት ነጥብ አሳክቷል
ኢትዮጵያ ቡናና ሀበሻ ቢራ ውላቸውን አደሱ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?