By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በአቶ ሠለሞን አባተ ላይ ያለውን ቅሬታ ገለፀ
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
ሀዋሳ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሲዳማ ቡና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በአቶ ሠለሞን አባተ ላይ ያለውን ቅሬታ ገለፀ

hatricksport team
hatricksport team 5 years ago
Share
SHARE

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባለፈው ሳምንት ለንባብ በበቃው ጋዜጣችን በቀን 23/2013 በቁጥር 655 The Big Interview በሚለው አምዳችን የብሔራዊ ፌዴሬሽኑ የቴክኒክ ኮሚቴ አባልና የአዲስ አበባ እግር ኳስ አሰልጣኞች ማህበር ዋና ፀሐፊ የሰጡትን ቃለ ምልልስ ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተሰማውን ቅሬታ በቀን 29/01/13 ዓ.ም በቁጥር 2/ኢ.እ.ፌ.አ.3/1806 በጽ/ቤት ኃላፊው በአቶ ባህሩ ጥላሁን ልመንህ ተፈርሞ በተፃፈ ደብዳቤ ገልፀውልናል፡፡

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለሌሎችም ምሣሌ በሚሆን መልኩ የፕሬስ ሕጉ የሚፈቅደውንና ሃሣብን በሃሣብ የመታገል የሰለጠነ መንገድ በጉዳዩ ዙሪያ የቀረበውን ቅሬታ በዝግጅት ክፍላችን አንዳችም የአርትኦት ስራ ሣይደረግበት እንዳለ ማቅረባችንን እየገለፅን ፌዴሬሽኑ ለመረጠው የሰለጠነ መንገድ ያለንን አድናቆት ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ ፌዴሬሽኑ ለዝግጅት ክፍላችን የላከው የቅሬታ ደብዳቤ ከዚህ በታች ቀርቧል፡፡


ለሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡- የጋዜጣ ቁጥር 655 ቅዳሜ መስከረም 23 2013 ዓ.ም ዕትም ይመለከታል

ከላይ በርዕሱ እንደተገለፀው ቅዳሜ መስከረም 23 ቀን 2013 ዓ.ም ለንባብ ባበቃችሁት ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ላይ አቶ ሰለሞን አባተ ከጋዜጣችሁ ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን በማስመልከት የሰጡት አስተያየት ከልብ አሳዝኖናል ብሎም አሳፍሮናል፡፡
በጋዜጣው ላይ ጠቅላላ ጉባኤ አምኖባቸው ወደ አመራርነት የመጡትን ሥራ አስፈፃሚዎቻኝን በተለይ የፕሬዚዳንታችንን ክብር የሚነኩ ከአንድ ሙያተኛ ነኝ ብሎ ከሚያምን ግለሰብ የማይጠበቅ አገላለጾችን በመጠቀም ተቋሙ ብሎም አመራሮቻችን በማህበረሰቡ ዘንድ የተዛባ እምነት እንዲያሳድር የሚያደርግ አሳሳች ተግባር ፈፅመዋል፡፡
ብሎም በአሁን ሰዓት በዝግጅት ያለው ሀገራችንን በመወከል የሚወዳደረው የብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን አባላቶቻችንን ህልውናውን ጠብቀን ውጤት እንዲያመጣ የስነ-ልቦና ዝግጅትንም ጭምር በማድረግ ላይ እያለ የቡድኑን የስነ ልቦና ዝግጅቱን የሚያደፈርስ ውጤት በማምጣት ላይ ከባድ ተፅዕኖ ሊያመጣ የሚችል ስሜታቸውን የሚጎዳ የተጫዋቾቻችንን የቡድን መንፈስ የሚያፈርስ የስፖርቱን እድገት ወደ ኋላ የሚጎትት አገላለጾችን ተጠቅመዋል፡፡
በመሆኑም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይህንን የስም ማጥፋት እንዲሁም የብሔራዊ ቡድኑን ስነ ልቦና የማናጋት ተግባር የፈፀሙትን ግለሰብ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት በመውሰድ በአፅንኦት የሚከታተለው መሆኑን እየገለፅን፣ በጋዜጣው ላይ ቃለ መጠይቅ የሰጡት ግለሰብ እየመጣ ያለው ለውጥን ወደ ኋላ ለመጎተት የተደረገ ስም ማጥፋት እንደሆነ ጋዜጣው እንዲያውቅልን እናሳስባለን፡፡

- ማሰታውቂያ -

ከሠላምታ ጋር
ባህሩ ጥላሁን ልመንህ
የጽ/ቤት ኃላፊ
ከማይነበብ ፊርማ ጋር

 

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By hatricksport team
Follow:
Hatricksport team
Previous Article “ለብሔራዊ ቡድን ከተጠሩት 41 ተጨዋቾች ውጪ መሆኔ በጣም አበሳጭቶኛል”ፈቱዲን ጀማል
Next Article ሃትሪክ…ሃትሪክ….ሀትሪክ…. በአንድ ቀን ማድረግ የማይቻለው የድርጊት ጉዟችን ቀጥሏል….

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

ረጀብ ሚፍታህ ፣ነፃነት ገብረመድህን፣ ቢኒያም ገነቱ፣ ምኞት ደበበ እና አህመድ ሁሴን የጨዋታ እገዳ ሲጣልባቸው እንዲሁም በክለቦች ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ቡና እና ባህር ዳር ከተማ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

Fitsum Nigusse By Fitsum Nigusse 11 months ago
ሰበታ ከተማ አምስት ተጫዋቾችን አስፈርሟል!!
የጨዋታ ዘገባ | የጦና ንቦቹ ከስምንት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል
ኮልፌ ቀራኒዮ ከ ጅማ አባጅፋር | ቀጥታ የውጤት መግለጫ
ኢትዮጵያ ከ ደቡብ አፍሪካ | ቀጥታ የውጤት መግለጫ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?