የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
1. ኤፍሬም ኃይለማርያም (ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ) እሁድ ጥር 18 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር ባደረገው የ16ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 90+1 ኛ ደቂቃ ላይ የተጋጣሚን ተጫዋች በመማታት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 63 በተቁ 1 (ሠ) እና በተቁ 2 መሰረት 4 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 4000 /አራት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
2. ግሩም ሃጎስ (መቻል) በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ – መቻል
- መቻል – አዳማ ከተማ
- መቻል – ቅዱስ ጊዮርጊስ
- መቻል -ባህርዳር ከተማ
በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።
- ማሰታውቂያ -
3. ብርሃኑ አዳሙ(ስሁል ሽረ) የ ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ስሁል ሽረ – ድሬደዋ ከተማ
- ኢትዮጵያ ቡና – ስሁል ሽረ
- ቅዱስ ጊዮርጊስ – ስሁል ሽረ
- ስሁል ሽረ – አርባምንጭ ከተማ
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ስሁል ሽረ
በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።
4. ብሩክ እንዳለ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- መቻል – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ኢትዮጵያ መድን
- ሲዳማ ቡና – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ኢትዮ ኤሌትሪክ
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ስሁል ሽረ
በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።


