የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
1. ሪችሞንድ አይ (ምድረ ገነት ሽረ ) : ክለቡ ከ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ጋር ባደረገው የ22ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 6ዐ ኛ ደቂቃ ላይየተጋጣሚን ቡድን ግልፅ የግብ የማግባት ዕድል በማበላሸት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ።
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 63 በተቁ 1 (ሐ) እና በተቁ 2 መሰረት 3 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺህ/ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
2. ቴውድሮስ ታፈሰ (ወላይታ ድቻ) : ክለቡ ከ ሃዋሳ ከተማ ጋር ባደረገው የ22ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 90+4 ኛ ደቂቃ ላይሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ።
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
3. ሽመልስ እንዳለ (ሀዲያ ሆሳዕና) /ወጌሻ/: ክለባቸው ከ አዳማ ከተማ ጋር ባደረገው የ22ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 22 ኛ ደቂቃ ላይሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀማቸው በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገዱ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦባቸዋል ።
ስለሆነም የቡድን አመራሩ ለፈፀሙት ጥፋት በፕሪምየር ሊግ የውድድር ደንብ ክፍል 1 አንቀፅ 13 ንዑስ አንቀጽ 13.3 ተቁ 15 መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገዱ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 6000/ስድስት ሺ/ እንዲከፍሉ የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
4. ቴዎድሮስ አጨ (አርባምንጭ ከተማ) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- አርባምንጭ ከተማ-ኢትዮጵያ ቡና
- አርባምንጭ ከተማ-ሃዋሳ ከተማ
- አርባምንጭ ከተማ-መቻል
- ምድረ ገነት ሽረ -አርባምንጭ ከተማ
- አርባምንጭ ከተማ-ኢትዮ ኤሌትሪክ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 15ዐዐ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
5. ማንያዘዋል ካሳ (ባህርዳር ከተማ): ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ባህርዳር ከተማ-ኢትዮጵያ መድን
- መቻል-ባህርዳር ከተማ
- ሲዳማ ቡና-ባህርዳር ከተማ
- ባህርዳር ከተማ-ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
- ኢትዮጵያ ቡና-ባህርዳር ከተማ
ስለሆነም ተጨዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
6. አብነት ደምሴ (ሃዋሳ ከተማ) : ከታች በተከቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ድሬደዋ ከተማ ሃዋሳ ከተማ
- ምድረ ገነት ሽረ-ሃዋሳ ከተማ
- ሃዋሳ ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስ
- ሃዋሳ ከተማ-ሲዳማ ቡና
- ወላይታ ድቻ-ሃዋሳ ከተማ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
7. ሙሴ ከበላ (ሀዲያ ሆሳዕና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ሀዲያ ሆሳዕና-ኢትዮጵያ መድን
- ሀዲያ ሆሳዕና-ሲዳማ ቡና
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ-ሀዲያ ሆሳዕና
- ፋሲል ከነማ ሀዲያ ሆሳዕና
- ሀዲያ ሆሳዕና-አዳማ ከተማ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
8. ዮሴፍ ዮሀንስ (ሲዳማ ቡና) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ-ሲዳማ ቡና
- ሲዳማ ቡና-መቐለ 70 እንደርታ
- ሲዳማ ቡና-ኢትዮጵያ ቡና
- ሲዳማ ቡና-ፋሲል ከነማ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
9. ካርሎስ ዳምጠው (ወላይታ ድቻ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- መቻል-ወላይታ ድቻ
- ኢትዮ ኤሌትሪክ -ወላይታ ድቻ
- ድሬደዋ ከተማ-ወላይታ ድቻ
- ወላይታ ድቻ-ሃዋሳ ከተማ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 15ዐዐ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
10. ኪሩቤል ወንድሙ (ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ-ሲዳማ ቡና
- ምድረ ገነት ሽረ -ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ
- ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ-አዳማ ከተማ
- ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ-ሸገር ከተማ
- ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ-ምድረ ገነት ሽረ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 15ዐዐ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
11. ምድረ ገነት ሽረ : ክለቡ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ጋር ባደረገው የ22 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የምድረ ገነት ሽረ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- ሪችሞንድ አይ *2
- አቤል መዝገበ
- ሽመክት ጉግሳ
- አዲሱ ተስፋዬ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 65 (ሀ) መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 / አምስት ሺ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
12. ወላይታ ድቻ :ክለቡ ከሃዋሳ ከተማ ጋር ባደረገው የ22 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የወላይታ ድቻ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- ኤፍሶን ኪዳነ
- ካርሎስ ዳምጠው
- ካዲሚ ዲያዬ
- ቴውድሮስ ታፈሰ
- ዮናታን ኤልያስ
- ቴውድሮስ ታፈሰ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 65 (ሀ) መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 / አምስት ሺ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
13. ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ : ክለቡ ከምድረ ገነት ሽረ ጋር ባደረገው የ22 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- ስምዖን ማሩ
- ኪሩቤል ወንድሙ
- ሙታክብዋ ጆኤል
- ሰመረ ሀፍተይ
- ኤፍሬም ኃ/ማርያም
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 65 (ሀ) መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
14. ሀዲያ ሆሳዕና : ክለቡ ከአዳማ ከተማጋር በነበረው የ22ኛ ሳምንት ግጥሚያ የክለቡ የቡድን አመራሮች 3 የቢጫ ካርድ ስለመመልከታቸው ሪፖርት ቀርቦበታል። ስለሆነም የቡድን አመራሮቹ በፈጸሙት ጥፋት በፕሪምየር ሊግ የውድድር ደንብ ክፍል 1 አንቀፅ 13 ንዑስ አንቀጽ 13.3 ተራ ቁጥር 17መሰረት ክለቡ ብር 10,000 / አስር ሺህ / እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
አስተያየት ይስጡ