የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
1. ሰመረ ሀፍተይ (ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ) : ክለቡ ከ ሸገር ከተማ ጋር ባደረገው የ16ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 70 ኛ ደቂቃ ላይየተጋጣሚን ተጫዋች በመማታት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ።
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 63 በተቁ 1 (ሠ) እና በተቁ 2 መሰረት 4 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000/ሶስት ሺህ/ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
2. ቡልቻ ሹራ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ጋር ባደረገው የ16ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 82 ኛ ደቂቃ ላይሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የየውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።


