By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ቁልቁል ገደልን እየናፈቀ የሚገኘው አርባምንጭ ከተማ …?
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሲዳማ ቡና
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችአርባምንጭ ከተማ

ቁልቁል ገደልን እየናፈቀ የሚገኘው አርባምንጭ ከተማ …?

ቴዎድሮስ ታከለ
ቴዎድሮስ ታከለ 1 month ago
Share
SHARE

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ስማቸውን በጉልህ ማፃፍ የቻሉ ስመ ጥር ተጫዋቾችን እንካችሁ በማለት ከሚታወቁ ጥቂት የሀገራችን አካባቢዎች መካከል አርባምንጭ ከተማ እና ዙሪያዋ ይጠቀሳሉ። በ80ዎቹ መጨረሻ አርባምንጭ ጨርቃ ጨርቅ በሚል ብቅ ብሎ ከብዙሀኑ ጋር የተዋወቀ ክለብ ቢመጣም የኋላ ኋላ የመፍረስ አደጋ ገጥሞት ደብዛው ጠፋ በመጨረሻም ዘለግ ካሉ አመታት በኋላ ግን አካባቢውን ዳግም በሚያስታውስ መልኩ አርባምንጭ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በሚል ተመስርቶ በ2004 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ መሳተፍ ቻለ። ቡድኑ ስድስት አመታትን ብቻ በፕሪምየር ሊጉ ከቆየ በኋላ በ2010 በአሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያም ዓመቱን ጀምሮ ፣ በረከት ደሙን በጊዜያዊ አሰልጣኝነት አቆይቶ ፣ የአሁኑ የንብ አሰልጣኝ እዮብ ማለ (አሞካቺን) አስከትሎ በመጨረሻም በአሁኑ የጋሞ ጨንቻ አሰልጣኝ ማቲዮስ ለማ እና የቀድሞው የክለቡ ግብ ጠባቂ ጃክሰን ፊጣ አማካኝነት በትግግዝ ከተመራ በኋላ በመጨረሻም በሊጉ መቆየት ሳይችል ለመውረድ ተገደደ።

በርካታ ተጫዋቾችን ለተለያዩ ክለቦች በማበርከት ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብስራት መሆን የቻለው አርባምንጭ ከተማ በቡድኑ ውስጥ በጊዜው የነበረው ጣልቃ ገብነት ፣ አሰልጣኞች ላይ የሚደረገው ስርሰራ በአግባቡ ስራዎችን እንዳይሰሩ በማድረግ በጥቅሉ በነበሩ መጠላለፎች ክለቡ ለመውረድ ዋነኛው ምክንያቶቹ ነበሩ። በአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ መሪነት ከከፍተኛ ሊጉ 2013 ላይ ማደጉን አረጋግጦ በድጋሚ በ2014ቱ ፕሪምየር ሊግ ላይ ለመሳተፍ የበቃው ክለቡ በደስታ ጮቤ በሽልማቶች ተንበሽብሾ ፕሪምየር ሊጉ ላይ ቢመጣም ባደገበት አመት አሁንም በቡድኑ ውስጥ የሚታዩ የመከፋፈል ስራዎች ፣ ጣልቃ ገብነቶች ፣ የክለቡ አመራሮች በማይመለከታቸው መግባት መቻላቸው ፣ እከሌን ያዝልኝ በሚል መደናቆር በቡድኑ ውስጥ በሚፈጠሩ ሌሎች ውስብስብ ችግሮች 2015 ላይ ከመሳይ ተፈሪ መሰናበት በኋላ በአሰልጣኝ በረከት ደሙ አማካኝነት አመቱን ቢያጠናቅቅም የጠቅስኳቸው ችግሮች ከሜዳ ላይ ውጤት ጋር ተደማምረው ለመውረድ ተገደደ።

በ2016 በከፍተኛ ሊጉ ላይ ለሦስተኛ ጊዜ ተከፋይ በመሆን በ2017 ተመልሶ በፕሪምየር ሊጉ ላይ መወዳደር ቢችልም ጆሮ ዳባ ልበስ ተብሎ መቅረት የነበረበት ችግሮቹ አብረውት ቀጥለው ቡድኑ እየተንገዳገደም ቢሆንም አመቱን ቋጭቶ ለዚኛው የውድድር ዘመን ፈተናዎችን በጭላንጭል ማለፍ ቻለ። አሰልጣኝ በረከት ደሙ ከሐምሌ 2017 ጀምሮ በተጫዋች ዝውውር ላይ ለመሳተፍ የተጫዋቾችን ስም ዝርዝር ቢያሳውቁም የክለቡ አመራሮች ከመምህርት በአንዴ ቴክኒክ ሀላፊ መሆን በቻለ ሰው ዝውውሩ መታየት አለበት በሚል ሰበብ በአሰልጣኙ ስራ ላይ ክረምት የጀመረው ጣልቃ ገብነት በፕሪምየር ሊጉ ላይ እየተባበሰ ቀጥሎ ቡድኑ እንዲከፋፈል በሚያደርጉ ሀሳቦች ፣ የመስራት ነፃነቶች አለመኖራቸው ፣ ሁሉም የስራ ድርሻውን ለይቶ አለማወቁ እና ሌሎችም በርካታ ውስብሶች አመታትን ተሻግረው ዛሬም ተጉዘው መቀረፍ ሳይችሉ አሰልጣኝ በረከትን በማሰናበት በቀድሞው ተጫዋቹ አበባው ቡጣቆ ቢመራም በዚህኛው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ቡድኑ ካደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በ8 ተሸንፎ በ8 አቻ ወጥቶ 17 ጎል ተቆጥሮበት 5 ብቻ አግብቶ በ12 የግብ ዕዳ በ8 ነጥብ ምንም ጨዋታ ማሸነፍ ሳይችል በደረጃ ሰንጠረዡ ግርጌ 20ኛ ላይ ተቀምጦ ይገኛሉ።

አራት ክለቦች በሚወርዱበት በዚህ አመት 19ኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘው ወልዋሎ በ5 ነጥብ ርቆ የሚገኘው ክለቡ በሜዳ በመከላከልም ይሁን በማጥቃት ያለበት ቴክኒካዊ ስህተቶች አርሞ በይበልጥ በማሸነፍ ዕሳቤ ውስጥ ሆኖ አሸናፊየት በመላበስ ማስተካከል ካልቻለ ሽንፈትን ልምምዱ እያደረገ መጓዙን ከቀጠለ ቡድኑ ውስጥ ያሉ ጣልቃ ገብነቶች ህግን የተከተሉ መሆን ካልቻሉ ገደል አፋፍ ላይ ቆሞ የሚገኘው ክለቡ አፋፉን አልፎ ቁልቁል ተንደርድሮ መግባቱ የሚቀር አይመስልም።

- ማሰታውቂያ -

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
Previous Article የ16ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Next Article አርባምንጭ ከተማ አዲስ አሰልጣኝ ለመሾም ከጫፍ ደርሷል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችሀዲያ ሆሳዕናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

የሀድያ ሆሳዕና የፋይናንስ ሃላፊ በዋስ ተለቀቁ

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 5 years ago
የጨዋታ ዘገባ | ላለመዉረድ እየታገሉ የሚገኙት አዳማ እና ድሬዳዋ ጨዋታቸውን በአቻ ዉጤት አጠናቀዋል !!
ሀትሪክ ስፖርትን ነገ በማለዳ  ይጠብቋትዘወትር ማክሰኞ ለንባብ የምትበቃው ተወዳጇ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገ በማለዳም የተለያዩ የሀገር ውስጥና የባህር ማዶ ስፖርት ዘገባዎችን ለንባብ ታቀርብሎታለች
የጨዋታ ዘገባ | ሀዋሳ ከተማ የመጀመሪያ ድሉን አሳክቷል
ፉአድ ፈረጃ የጣና ሞገዶቹን ተቀላቅሏል!!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?