የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
1. ሱልጣን በርሄ (ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ) : ሰኞ ታህሳስ 20 2018 ዓ.ም. ክለቡ ከ ባህርዳር ከተማ ጋር ባደረገው የ12ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 33 ኛ ደቂቃ ላይሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ።
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የየውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
2. ቢኒያም ካሣሁን (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) : ረቡዕ ታህሳስ 22 2018 ዓ.ም. ክለቡ ከ ኢትዮጵያ መድን ጋር ባደረገው የ12ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 73 ኛ ደቂቃ ላይሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ።
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የየውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
3. ሬድዋን ሸረፉ(ድሬደዋ ከተማ) በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድተመልክቷል።
- ማሰታውቂያ -
- ድሬደዋ ከተማ-ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ
- ድሬደዋ ከተማ-ሲዳማ ቡና
- ድሬደዋ ከተማ-አዳማ ከተማ
- ድሬደዋ ከተማ-ነገሌ አርሲ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
4. ንጋቱ ገ/ ስላሴ(ኢትዮጵያ መድን ): ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድተመልክቷል።
- ባህርዳር ከተማ-ኢትዮጵያ መድን
- ኢትዮጵያ መድን -ኢትዮ ኤሌትሪክ
- ሃዋሳ ከተማ-ኢትዮጵያ መድን
- ኢትዮጵያ መድን-ሲዳማ ቡና
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ-ኢትዮጵያ መድን
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
5. ፋሲል ከነማ ክለቡ ከኢትዮ ኤሌትሪክ ጋር ባደረገው የ12ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ የክለቡ ደጋፊዎች 50 የስታዲየሙን ወንበሮች ስለመሰባበራቸውና መንቀላቸው ሪፖርት ተደርጓል።
ስለሆነም ክለቡ ወንበሮቹን እንዲያሰራ ወይም የስታድየሙ ባለቤት አሰርቶ የሚያቀርበውን ዋጋ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
6. ነገሌ አርሲ ክለቡ ከ አዳማ ከተማ ጋር ባደረገው የ12ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ ከዕረፍት መልስ ጨዋታው 5 ደቂቃ ዘግይቶ ለመጀመሩ ምክኒያት ስለመሆኑ
ሪፖርት ተደርጓል፡፡
ስለሆነም ክለቡ ላጠፋው ጥፋት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የውድድርና ስነስርዓት የውድድር ደንብ ክፍል 1 አንቀጽ 13 ንዑስ አንቀጽ 13.2 በተራ ቁ. 17 እና 18 መሰረት ብር 15000/ አስራ አምስት ሺህ/ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
7. ናትናኤል ሰለሞን ( ነገሌ አርሲ ) ክለቡ ከ ድሬደዋ ከተማ ጋር ባደረገው የ12ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ ግብ ካስቆጠረ በኋላ ሀይማኖታዊ መልዕክት ያለው ምስል ከካልሲ ውስጥ በማውጣት ለካሜራ/ለተመልካች ስለማሳየቱ ሪፖርት ተደርጓል።
ስለሆነም ተጫዋቹ ላጠፋው ጥፋት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የውድድርና ስነስርዓት የውድድር ደንብ ክፍል 1 አንቀጽ 9 ንዑስ አንቀጽ 9.2 በተራ ቁ. 5 እና 6 መሰረት ተጫዋቹ ብር 3000/ሶስት ሺህ/ እንዲሁም ክለቡ ብር 10000 /አስር ሺህ /እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡


