የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
ሐብታሙ ሽዋለም (ኢትዮ ኤሌትሪክ ) ቅዳሜ ታህሳስ 26 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ባደረገው የ12ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 87 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
- ማሰታውቂያ -
አብዩ ካሣዬ (ድሬደዋ ከተማ) ቅዳሜ ታህሳስ 26 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከባህርዳር ከተማ ጋር ባደረገው የ12ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 5 ኛ ደቂቃ ላይ የተጋጣሚን ቡድን ግልፅ ግብ የማግባት ዕድል በማበላሸት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
እንየው ካሳሁን (ሃዋሳ ከተማ) አርብ ታህሳስ 25 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከፋሲል ከነማ ጋር ባደረገው የ12ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 45 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
ፍፁም ጥላሁን (ቅዱስ ጊዮርጊስ) በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ቅዱስ ጊዮርጊስ – ፋሲል ከነማ
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
- መቻል – ቅዱስ ጊዮርጊስ
- ቅዱስ ጊዮርጊስ – ኢትዮ ኤሌትሪክ
በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 10,000 /ኣስር ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።
ሃዋሳ ከተማ ክለቡ ከፋሲል ከነማ ጋር ባደረገው የ12 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የሃዋሳ ከተማ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- እንየው ካሳሁን
- በረከት ሳሙኤል
- ሰለሞን ወዴሳ
- አሊ ሱሌማን
- ወንድማገኝ ተሾመ
- እንየው ካሳሁን
- ቢንያም በላይ
- ዳዊት ታደሰ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
ድሬደዋ ከተማ ክለቡ ከባህርዳር ከተማ ጋር ባደረገው የ12 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የድሬደዋ ከተማ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- አብዩ ካሣዬ
- አህመድ ረሺድ
- ኢስማኤል አብዱል ጋኒዩ
- አቡበከር ሻሚል
- አላዛር ማረነ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለቡ ከኢትዮ ኤሌትሪክ ጋር ባደረገው የ12 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- አማኑኤል አረቦ
- ፍፁም ጥላሁን
- ቢንያም ፍቅሩ
- በረከት ወልዴ
- ሄኖክ ዮሀንስ
- አዳነ ግርማ
- ተመስገን ዮሃንስ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
መቐለ 70 እንደርታ ክለቡ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ባደረገው የ12 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የመቐለ 70 እንደርታ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- መድሃኔ ብርሀኔ
- ሔኖክ አንጃው
- ሙሉጌታ ወ/ጊዮርጊስ
- ሸሪፍ መሀመድ
- ዘረሰናይ ብርሃነ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡


