የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
1. ፍቅሩ አለማየሁ (ሸገር ከተማ) : ረቡዕ ኅዳር 17 2018 ዓ.ም. ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ7ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 58 ኛ ደቂቃ ላይሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀማቸው በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የየውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
2. አሰጋኸኝ ጴጥሮስ (መቐለ 70 እንደርታ) : ሐሙስ ኅዳር 18 2018 ዓ.ም. ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ባደረገው የ7ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 81 ኛ ደቂቃ ላይሆን ብሎ የተጋጣሚ ቡድንን ተጫዋች በክርን በመማታት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ።
- ማሰታውቂያ -
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 63 በተቁ 1 (ሠ) እና በተቁ 2 መሰረት 4 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3ዐዐዐ /ሶስት ሺህ / እንዲከፍል የየውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
3. መቻል ክለቡ ከሲዳማ ቡና ጋር ባደረገው የ7 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የመቻል ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- ኦሊዮንዚ ናፊያን
- አብዱልከሪም ወርቁ
- ግሩም ሃጎስ
- ቻላቸው መንበሩ
- ኮሊን ኮፊ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 65 (ሀ) መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
4. ሸገር ከተማ ክለቡ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ7 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የሸገር ከተማ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- አቡሽ ረጋሳ
- ፍቅሩ አለማየሁ*2
- ባህሩ ነጋሽ
- አቤል አየለ
- ሔኖክ አዱኛ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 65 (ሀ) መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
5. መቐለ 70 እንደርታ ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በነበረው የ7ኛ ሳምንት ጨዋታ በ2017 የውድድር ዘመን 36ኛ /የመጨረሻ ሳምንት / ጨዋታ በቀይ ካርድ የተወገደውንና 4 ጨዋታ እንዲታገድ የተወሰነበትን ሱሌማን ሃሚድ የተባለ ተጫዋች ያለፉትን 6 ጨዋታዎች አሰልፎ ስለማጫወቱ እና በዚህም የፎርፌ ውጤት ይገባኛል በማለት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ክስ ቀርቦበታል።
የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ የቀረበውን ክስ መነሻ በማድረግ ባካሄደው ማጣራት ተጨዋቹ ለመቐለ 70 እንደርታ በ2ኛ ሳምንት ከመቻል፣ በ3ኛ ሳምንት ከድሬዳዋ ከተማ እና በ4ኛ ሳምንት ከሃዋሳ ከተማ በተደረጉት ጨዋታዎች ቅጣቱን ሳይጨርስ ተሰልፎ እንደተጫወተ አረጋግጧል።
ስለሆነም ከለቡ / መቐለ 70 እንደርታ/ ተገቢ ያልሆነ ተጫዋች አሰልፎ በማጫወት ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 5 አንቀጽ 36(ሐ) መሰረት ከ2ኛ እስከ 4ኛ ሳምንት ያሉትን 3 ጨዋታዎች ውጤት ተሰርዞ በፎርፌ ተሸናፊ እንዲሆን (በሶስቱም ጨዋታዎች 0 ነጥብና 3 የግብ እዳ እንዲመዘገብበትና ፡ለተጋጣሚዎቹ መቻል፣ ድሬዳዋ ከተማ እና ሀዋሳ ከተማ 3 ነጥብና 3 ግብ እንዲመዘገብላቸው/ በተጨምሪም ብር ሃያ ሺህ /20 000/ እንዲከፍል እንዲሁም የቡድን መሪው 6 ወር እንዲታገድ የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
6. ነገሌ አርሲ ክለቡ ከ ኢትዮጵያ መድን ጋር በነበረው የ7ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ መርሃ ግብር የክለቡ ደጋፊዎች 2/ሁለት/ ወንበር ስለመስበራቸው ሪፖርት ተደርጓል፡፡ ስለሆነም ክለቡ የተሰበሩትን ወንበሮች እንዲያሰራ ወይም የስታድየሙ ባለቤት አሰርቶ የሚያቀርበውን ዋጋ እንዲከፍል ወስኗል፡፡
7. መቐለ 70 እንደርታ ክለቡ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በነበረው የ7ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ መርሃ ግብር የክለቡ ደጋፊዎች 41/አርባ አንድ/ የስታድየሙን ወንበሮች ስለመስበራቸው ሪፖርት ተደርጓል። ስለሆነም ክለቡ የተሰበሩትን ወንበሮች እንዲያሰራ ወይም የስታድየሙ ባለቤት አሰርቶ የሚያቀርበውን ዋጋ እንዲከፍል ወስኗል፡፡


