የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
1. ዳግም ንጉሴ (ሀዲያ ሆሳዕና): በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 2 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 8 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ሀዲያ ሆሳዕና – ወላይታ ድቻ
- ድሬደዋ ከተማ – ሀዲያ ሆሳዕና
- ሀዲያ ሆሳዕና -ሲዳማ ቡና
- አርባምንጭ ከተማ – ሀዲያ ሆሳዕና
- ሀዲያ ሆሳዕና – ባህርዳር ከተማ
- ወላይታ ድቻ – ሀዲያ ሆሳዕና
- ፋሲል ከነማ – ሀዲያ ሆሳዕና
- ኢትዮጵያ ቡና – ሀዲያ ሆሳዕና
በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35 (ሠ) መሰረት 2 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።
2. ካሌብ ኣማንክዋህ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
- ባህርዳር ከተማ – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
- ወላይታ ድቻ – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ወልዋሎ አዲግራት
በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።
- ማሰታውቂያ -

3. ተመስገን ተስፋዬ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ): የኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – መቐለ 70 እንደርታ
- ሀዲያ ሆሳዕና – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ሲዳማ ቡና
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ወልዋሎ አዲግራት
በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።
4. በረከት ግዛው (ፋሲል ከነማ): ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ቅዱስ ጊዮርጊስ – ፋሲል ከነማ
- ፋሲል ከነማ – አርባምንጭ ከተማ
- ፋሲል ከነማ – ኢትዮ ኤሌትሪክ
- ፋሲል ከነማ – ሃዋሳ ከተማ
- ስሁል ሽረ – ፋሲል ከነማ
በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ
ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።
5. ዮሴፍ ዮሀንስ (ሲዳማ ቡና) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ሲዳማ ቡና
- ሲዳማ ቡና-ባህርዳር ከተማ
- ኢትዮጵያ ቡና – ሲዳማ ቡና
- ሲዳማ ቡና – መቻል
በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት I ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።
6. አብዱልከሪም ወርቁ (መቻል) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- መቻል – ወላይታ ድቻ
- መቐለ 70 እንደርታ-መቻል
- መቻል – አርባምንጭ ከተማ
- ሲዳማ ቡና – መቻል
በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።
7. ሙሉቀን አዲሱ (ወላይታ ድቻ) : ክለቡ ከ አርባምንጭ ከተማ ጋር ባደረገው የ 28 ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ ሃይማኖታዊ መልእክት የሚያስተላልፍ ምስል በውስጥ ልብሱ ደርቦ ስለመልበሱ ሪፖርት ተደርጎበታል። በመሆኑም በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ደንብ ክፍል 1 አንቀፅ 9 ንዑስ አንቀፅ 9.2 ተቁ 4 እና 5 መሰረት ተጫዋቹ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺህ/ እንዲሁም ክለቡ የገንዘብ ቅጣት ብር 10000 /አስር ሺህ /እንዲከፍሉ ወስኗል፡፡
8. አቶ ገዛኸኝ ለማ /አዳማ ከተማ -ስራ አስኪያጅ/ ክለቡ ከመቐለ 70 እንደርታጋር በነበረው የ28ኛ ሳምንት ግጥሚያ በጨዋታው ወቅት የእለቱን ዳኞች በተደጋጋሚ አጸያፊ ስድብ ስለመሳደባቸው ሪፖርት ቀርቦባቸዋል ። ስለሆነም የክለቡ አመራር በፈጸመው ጥፋት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ደንብ ክፍል 10 አንቀፅ 35 በተቁ 2 መሠረት ከ29ኛ ሳምንት ጀምሮ አዳማ ከተማ የሚያደርጋቸውን 5/አምስት/ ተከታታይ ጨዋታዎች ስታድየም ገብተው እንዳይመለከቱ የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።


