የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
1. ሄኖክ ሀሰን (ድሬደዋ ከተማ): ረቡዕ መጋቢት 24 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከአዳማ ከተማ ጋር ባደረገው የ23ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 78 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
2. ብሩክ ማርቆስ (ሀዲያ ሆሳዕና): ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
ተጋጣሚዎች
- መቐለ 70 እንደርታ – ሀዲያ ሆሳዕና
- ሀዲያ ሆሳዕና – ፋሲል ከነማ
- ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ – ሀዲያ ሆሳዕና
- ሀዲያ ሆሳዕና – ባህርዳር ከተማ
- ቅዱስ ጊዮርጊስ – ሀዲያ ሆሳዕና
በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።
- ማሰታውቂያ -

3. ድሬደዋ ከተማ: ክለቡ ከአዳማ ከተማ ጋር ባደረገው የ23 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የድሬደዋ ከተማ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- አብዱልሰላም የሱፍ
- ሄኖክ ሀሰን
- አላዛር ማረነ
- ሄኖክ ሀሰን
- ጀሚል ያቆብ
- አህመድ ረሺድ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ እፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
4. አሰልጣኝ አትክልቲ በርሃ (ረዳት አሰልጣኝ) / ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በነበረው የ21ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ በውድድር አመቱ ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ ቢጫ ካርድ ተመልክተዋል። ስለሆነም በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ደንብ ክፍል 1 አንቀፅ 13.3 በተቁ 16 መሠረት አሰልጣኙ 1/አንድ/ ጨዋታ እንዲታገዱና ብር 5000 /አምስት ሺህ/ እንዲከፍሉ ወስኗል።
ጥሪ
አሰልጣኝ ተረፈ ሂርጳሳ (ድሬዳዋ ከተማ-ረዳት አሰልጣኝ) የፕሪምየር ሊግ ውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ሊያነጋግሮት ስለሚፈልግ እሁድ መጋቢት 28 2017 ጠዋት 4፡30 ስዓት ታደሰ እንጆሪ ሆቴል (ሀዋሳ-ቅድመ ስብሰባ በሚደረግት ቦታ) እንዲገኙ ጥሪውን ያስተላልፋል።


