ድሬዳዋ ከተማዎች አሁንም ተጫዋቾችን ማስፈረማቸዉን ሲቀጥሉ የተጠናቀቀውን የዉድድር አመት በክትፎዎቹ ቤት ያሳለፈዉን የመስመር አጥቂ ሄኖክ አየለ ወደ ስብስባቸዉ መቀላቀላቸው ተረጋግጧል።
ከዚህ ቀደም ለሲዳማ ቡና ፣ ደቡብ ፖሊስ ፣ ሀዋሳ ከተማ እንዲሁም የ2013 የዉድድር አመትን በወልቂጤ ከተማ ቤት ተጫዉቶ ማሳለፍ የቻለዉ አጥቂው የ2014 የዉድድር አመትን ከአሰልጣኝ ዘማርያም ወ/ጊዮርጊስ ስብስብ ጋር እንደምንመለከተው የክለቡ ድህረገጽ አስነብቧል።
አስተያየት ይስጡ