ከመስከረም 15 ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም እየተከናወነ የሚገኘዉ የአዲስአበባ ከተማ ዋንጫ ሁለተኛ የምድብ ጨዋታዎች ከነገ ጀምሮ መካሄዳቸዉን ይቀጥላሉ።
በምድብ አንድ የተደለደሉት አዲስአበባ ከተማ እና ጅማ አባጅፋር 8:00 ሰዓት ላይ ጨዋታቸዉን የሚያደርጉ ሲሆን ምድብ አንድን ከመከላከያ ጋር በእኩል ሶስት ነጥብ በመምራት ላይ የሚገኙት ተጋባዦቹ ጅማዎች የመጀመሪያ ጨዋታቸዉን ኢትዮጵያ ቡናን በዳዊት ፍቃዱ እና መሀመድ ኑር ግቦች ታግዘዉ ሁለት ለዜሮ ካሸነፉ በኋላ በነገዉ ዕለት ሌላኛዉን የመዲናዉን ክለብ አዲስአበባ ከተማ የሚገጥሙ ይሆናል።
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታም ቀን 10:00 ላይ የምድቡን የመጀመሪያ ጨዋታ በጅማ አባጅፋር የተሸነፉት ኢትዮጵያ ቡናዎች ከ ሌላኛው የከተማዉ ክለብ መከላከያ ጋር የሚጫወቱ ይሆናል። በመክፈቻ ጨዋታው በርከት ያሉ ወጣት ተጫዋቾችን የተጠቀሙት ቡናማዎቹ በነገዉ ዕለት የመጀመሪያ ሶስት ነጥባቸዉን ለማሳካት ከመከላከያ ብርቱ ፉክክር እንደሚጠብቃቸው የሚጠበቅ ሲሆን በአንፃሩ በአሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ የሚመሩት መከላከያዎች ደግሞ ሁለተኛ የምድብ ጨዋታቸዉንም በድል ለመወጣት ወሳኙን ግጥሚያ ከቡናማዎቹ ጋር የሚያደርጉ ይሆናል።
አስተያየት ይስጡ