መነሻ ገጽ ሰበታ ከተማ አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ ሰበታ ከተማን አስጠነቀቀ
ሰበታ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎች

አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ ሰበታ ከተማን አስጠነቀቀ

አጋራ
አጋራ

 

ውጤታማ ለመሆንና ተፎካካሪ ቡድን ለመገንባት የተጨዋቾችን ሞራል መገንባትና ፍላጎታቸውን ሟሟላት የግድ ነው ሲል ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ ለክለቡ ባስገባው ደብዳቤ አሳሰበ።

የክለቡ አመራሮች ረቡዕ ዕለት ተጨዋቾችን ሰብስበው ከመከሩ በኋላ ጥቅማጥቅሞችና ደመወዝ ገብቶላችኋል በማለት የክለቡ ፕሬዝዳንት ቢናገሩም ገንዘቡ ሳይገባ መቅረቱ ቅሬታ ፈጥሯል።
ሁኔታው እንዲስተካከል በቃል ሲጠይቅ የነበረው አሰልጣኝ አብርሃም በግልባጭ ለሊግ ካምፓኒውና ለፌዴሬሽኑ ባስገባው ደብዳቤ በዚህ ቅሬታ ውስጥ የሆኑ ተጨዋቾችን ይዤ ውጤት ማምጣት አልችልም ቃል ገብታችሁ አልፈጸማችሁም በዚህ መንገድ ጠንካራ ቡድን መፍጠር አልችልም ወደ ጅማም መሄድ ይከብደኛል በማለት ማሳሰቢያ መስጠቱ ታውቋል።

ከአመራሮቹ ጋር በተካሄደ ውይይት ላይ ኳስ ወደ ኋላ እየመለሳችሁ ነው በማለት ፕሬዝዳንቱ የሰጡት አስተያየት ግርምትን ፈጥሯል። አሰልጣኙ ይሄን ጉዳይ ለኛ ተዉልን የሚመስል አስተያየት ሰጥቷል ተብሏል በአንድ ጨዋታ ከ600 በላይ ፓስ ያደረገው ቡድኔ ነው በማለት ፕሬዝዳንቱን ወረፍ አድርጎል።

ከዚያም ውጪ በኔ ስልጠናና አጨዋወት የማታምኑ ካላችሁ አሁኑኑ መለያየት እንችላለን በማለት ቆፍጠን ያለ ምላሽ መስጠቱ ታውቋል። የኔን ገንዘብ አስገቡልኝና ወደ ስራዬ ልግባ የሚል ግለኛ አሰልጣኝ በበዛበት እግር ኳስ አሰልጣኝ አብርሃም የልጆቹን ገንዘብ በቅድሚያ አስገቡ ማለቱም ታውቋል። የአሰልጣኙ ቆራጥ አቋም አስድንግጧቸው ይሁን አይሁን ባይታወቅም አመራሮቹ ለአዲስ ፈራሚዎች ካላቸው የ6ወር ደመወዝ የ4ቱን የነባሮቹን ደግሞ የታህሳስን ደመወዝ በመክፈል ቅሬታውን ለማለዘብ ሞክረዋል። ያም ቢሆን ደስተኛ ያልሆኑ ተጨዋቾች እንዳሉ የተረዳው አሰልጣኝ አብርሃም ከ5ቀን በኋላ ትላንት ተሰባስበው በሰሩት ልምምድ ላይ ሳይገኝ ቀርቷል።

ቡድኑ ዛሬ የኮቪድ 19 ምርመራ በማድረግና ቀለል ያለ ልምምድ በማድረግ ነገ ከሰአት ወደ ጅማ ተጉዞ አርብ 9 ሰአት ወላይታ ድቻን የሚገጥም
መሆኑ ታውቋል። በአስተዳደራዊ ችግር ምክንያት 5ቀን ልምምድ ሳይሰሩ ውጤት ቢጠፋ ሌላ ውዝግብ እንዳይፈጥር ተሰግቷል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...