መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ኮቪድ መጥፎ ጥላውን ያጠላበት የሲዳማ ቡናና የአዳማ ከተማ ጨዋታ ፈተና ውስጥ ወድቋል ከሁለቱም ቡድን ከ31 ተጫዋች በላይ እንደተያዙ እየተነገረ ነው ፎርፌ ይሰጣል?ወይስ ጨዋታው ይተላለፋል?
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ኮቪድ መጥፎ ጥላውን ያጠላበት የሲዳማ ቡናና የአዳማ ከተማ ጨዋታ ፈተና ውስጥ ወድቋል ከሁለቱም ቡድን ከ31 ተጫዋች በላይ እንደተያዙ እየተነገረ ነው ፎርፌ ይሰጣል?ወይስ ጨዋታው ይተላለፋል?

አጋራ
አጋራ

የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ቀን ውድድር ዛሬ በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ማለትም በ10:00 ሠዓት ባህር ዳር ከተማና ወልቂጤ እንዲሁም በ1:00 ሲዳማ ቡናና አዳማ ከተማ በሚያደርጉት ጨዋታ እንደሚከናወን መርሀ ግብር ቢያዝለትም በተለይ የሲዳማ ቡናና የአዳማ ከተማ ጨዋታ መካሄዱ አጠራጣሪ ሆኗል።

የዚህ ምክንያቱ ደግሞ ከ31 የሚበልጡ ተጫዋቾች የኮቪድ-19 ምልክት ታይቶባቸዋል የሚል የምርመራ ውጤት በመቅረቡ ጨዋታው ጥያቄ ውስጥ እንዲወድቅ አድርጎታል። እንደ መረጃ ምንጮቻችን ከሆነ ሲዳማ ቡና ካለው 32 የቡድኑ አባላት በ27ቱ ላይ የኮቪድ-19 ምልክት እንደተገኘባቸው የምርመራ ውጤቱ የሚገልፅ ሲሆን በአዳማ ከተማ በኩል ደግሞ 21 ተጫዋቾች ላይ በተመሳሳይ ምልክቱ መገኘቱ ነው የተጠቆመው።

የሁለቱም ቡድን አባላትና አመራሮች በተፈጠረው ነገር ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ የገቡ ሲሆን በድሬዳዋ ያደረጉትን የምርመራ ውጤት በመጠራጠርና ይሄ ሁሉ ተጫዋች ሊያዝ አይችልም በማለት ትናንት ምሽት በድጋሚ ሀረር ሄደው ምርመራ ማድረጋቸውና ውጤቱን እየተጠባበቁ እንደሆነ ታውቋል። ከሰዓታት በሃላ ጨዋታቸውን የሚያደርጉት የሁለቱ ክለቦች በሀረር ያደረጉት የሁለተኛ ምርመራቸው ውጤት ለጨዋታ የሶስት ሠዓት እድሜ ሲቀራቸው የሚታወቅ ሲሆን ከዚያ በሃላ በምን አይነት ስነ ልቦና ወደ ሜዳ ገብተው ሊጫወቱ ይችላሉ?የሚለው ከወዲሁ አሰጨናቂ ሆኗል።

ኮቪድ መጥፎ ጥላውን ያጠላበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ መጨረሻን ብዙዎች በጉጉት እየጠበቁት ሲሆን ጨዋታው ይተላለፋል? ወይስ ፎርፌ ይሰጣል?ከሁለቱም በርካታ ተጫዋች ተይዞ ፎርፌ የሚሰጠው ለማን ነው? የሚለው ብዙዎች ጆሮአቸውን አቁመው ለመስማት የሚፈልጉት አንኳር ጥያቄ ሆኗል

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...