የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ በትላንትናው ዕለት በ ድሬደዋ ከተማ አንድ ብሎ መካሄዱን ሲጀምር ተጫዋቾች በከፍተኛ ሁኔታ የቫይረሱ ተጋላጭ እየሆኑ ይገኛሉ ።
ሀትሪክ ስፖርት ባገኘችው መረጃ መሰረት አብዛኛው ክለብ የዋና ቡድን ተጫዋቾቻቸው በስፋት እየተያዙባቸው ይገኛል ።
ከነዚህም መካከል :-
1. ወላይታ ድቻ – ስምንት ተጫዋቾች
2. ሐዋሳ ከተማ – ሰባት ተጫዋቾች
3. ባህርዳር ከተማ – አራት ተጫዋቾች
4. ቅዱስ ጊዮርጊስ – ሶስት ተጫዋቾች
5. ሰበታ ከተማ – ሙሉ የቡድን አባላቱ ከቫይረሱ ነፃ
6. አዳማ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ምንም እንኳ ቁጥሩን ማረጋገጥ ባይቻልም ቁጥራቸው ከፍ ያለ ተጫዋቾች በቫይረሱ መያዛቸውን ከውስጥ ምንጮች ለማወቅ ችለናል ።
ሲዳማ ቡና እንዲሁም ጅማ አባ ጅፋር እግር ኳስ ክለብ ምርመራው ተደርጓላቸው ውጤት በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ክለቦች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል ።
አስተያየት ይስጡ