ኢትዮጵያ በመወከል በቻን ውድድር ላይ የሚገኘው ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ ዛሬ ምሽት የሚደረገውን ተጠባቂ ጨዋታ ይመራል።
ጨዋታው በሴኔጋል እና ናይጄሪያ መካከል በዛንዚባር አማን ስታድየም ከምሽት 2:00 ጀምሮ የሚደረግ ነው።
ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ በጨዋታው ላይ በረዳት የቫር ዳኝነት ነው የተመደበው።
በዋና የቫር ዳኝነት ግብፃዊው መሀሙድ አሾር ተሰይሟል።
- ማሰታውቂያ -
ጨዋታውን ግብፃዊው መሐመድ አህመድ ናጊ ሞሳ በዋና ዳኝነት ሲመራው የኤርትራ የጅቡቲ ዜግነት ያላቸው ረዳት ዳኞች አብረውት ጨዋታውን ይመራሉ።



