በሊጉ ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች ከአዞዎቹ ጋር ልምምድ እየሰሩ ናቸው።
አሰልጣኝ አዲሴ ካሳን ከቀጠረ በኋላ በአራት ጨዋታዎች ሽንፈት ያልቀመሰው እና ሁለት አሸንፎ ሁለት አቻ የወጣው አርባምንጭ ከተማ ሁለት ተጫዋቾችን ለማስፈረም በልምምድ ላይ እየመለከተ ይገኛል።
የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ ፣ መቻል ፣ አራት አመታትን ደግሞ በፋሲል ከነማ ያሳለፈው እንዲሁም ያለፈውን አመት በኢትዮ ኤሌክትሪክ የነበረው አጥቂው ፍቃዱ አለሙ ጥቂት ጊዜን በዕረፍት ካሳለፈ በኋላ አርባምንጭን ለመቀላቀል ከክለቡ ጋር ልምምድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሌላኛው የቀድሞው የድሬዳዋ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ላለፉት ስድስት ወራት በአቃቂ ቃሊቲ የነበረው ተከላካዩ አማረ በቀለ ከክለቡ ጋር ልምምድ እየሰሩ የሚገኝ ሲሆን ጥሩ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴን ካሳዩ በይፋ ክለቡን ይቀላቀላሉ ተብሎ ይጠበቃል።


