ከደቂቃዎች በፊት ጋናዊው አጥቂ ያስፈረሙት አዞዎቹ ሴኔጋላዊውን ተጫዋች አራተኛ ፈራሚ አድርገዋል።
የቀድሞው የተከላካይ አማካይ ስፍራ ተጫዋቾቻቸው ናይጄሪያዊውነሰ ቻርለስ ሪቫኑን ለማስፈረም ጥረት አድርገው ሳይሳካላቸው የቀሩት አርባምንጭ ከተማዎች ከፍቃዱ አለሙ አማረ በቀለ እና ከሰዓታት በፊት ከነገርኳችሁ ጋናዊው አጥቂ መሐመድ አብዱል ራህማን ቀጥሎ አራተኛው የጥር አዲስ ፈራሚ ሴኔጋላዊው የ29 አመት የተከላካይ እና የአጥቂ አማካይ ቦታ ተጫዋቹ ማማዱ ሴክ ሆኗል።
ከሀገሩ ክለብ ጉዲአዋይ የክለብ ህይወቱን ከጀመረ በኋላ ፣ ጀነሬሽን ፉት ፣ ኒዲያን ቡር ፣ ተውን ጉዝኤ እና ኤስ ጃራፍ ግልጋሎት ሰጥቶ ለሞሮኮው ሞግ ህርብ ለታንዛኒያው ኤ ኤስ ቪታ እንዲሁም በያዝነው አመት ለሲሪያው ክለብ ኤ ኤስ ፉቱዋ እየተጫወተ የሚገኘው ተጫዋቹ ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ መጥቶ የአዞዎቹ ንብረት ለሊቱን መሆኑን ያረጋግጣል።
አስተያየት ይስጡ