የ2016 ዓ/ም በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የውድድር ዘመን ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ አህመድ ሁሴን በአርባምንጭ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ጋር የሚያቆየውን ውል ለመፈረም ተስማማ ።
ክለቡ በ2017 ዓ/ም በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ ለመቅረብ ነባር የክለቡ ተጨዋቾችን ውል የማደስ ስራ አሁንም አጠናክሮ ቀጥሏል።
በወጣቱ ዋና አሰልጣኝ በረከት ደሙ እየተመራ የከፍተኛ ሊጉ የአሸናፊዎች አሸናፊ ክለብ አርባምንጭ ከተማ እግር ኳስ ክለብ በፕሪሚየር ሊጉም ጥንካሬውን ለማስቀጠል የክለቡ ነባር ተጨዋቾችን ውል የማደስ ስራ እየሰራ መቆየቱ ይታወሳል ፤ በዛሬው ዕለትም የክለቡ የጎል ማሽኑ አህመድ ሁሴን በክለቡ ለመቆየት ከስምምነት ላይ ደርሷል ።



