በተጠናቀቀዉ የውድድር አመት በአሰልጣኝ ነፃነት ክብሬ እየተመራ በሶስተኛ ደረጃነት ሊጉን ያጠናቀቀው እና የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ መሆን የቻለዉ ኢትዮጵያ ቡና ለቀጣዩ የውድድር አመት ራሱን አጠናክሮ ለመቅረብ ተጫዋቾችን ወደ ስብስቡ መቀላቀሉን ቀጥሏል።
አማኑኤል ዮሐንስ እና አብዱልከሪም ወርቁ ከመሳሰሉ ወሳኝ ተጫዋቾቹ ጋር የተለያየዉ እና በተቃራኒው በርከት ያሉ ተጫዋቾችን ወደ ስብስቡ በመቀላቀል ላይ የሚገኘዉ ኢትዮጵያ ቡና አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ላይ ድንቅ ጊዜ ከፉሪ ክፍለ ከተማ ጋር ማሳለፍ የቻለዉን ወጣቱን የፊት መስመር አጥቂ ሀብታሙ አሸናፊ በአራት አመት የኮንትራት ውል ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።
አጥቂዉ ከቀናት በፊት በድሬዳዋ ከተማ በተከናወነዉ የኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ላይ በስድት ጨዋታዎች 11 ጎሎችን በማስቆጠር ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሆኖ ማጠናቀቁ ይታወሳል።



