የአርባምንጭ ከተማው የፊት አጥቂ አህመድ ሁሴን ቡድኑ ከመቀሌ 70 እንደርታ ባደረገው ጨዋታ ላይ ጉዳት ማስተናገዱ ይታወሳል።
በ89ኛው ደቂቃ ላይ ከቀኝ መስመር የተሻገረለትን ኳስ ለማስቆጠር በሚያደርገው ጥረት ጉዳቱን ያስተናገደው አጥቂው ጨዋታውን ለመጨረስ ሳይችል ቀርቷል።
በጨዋታው ላይ የቡድኑን ቀዳሚ ግብ አስቆጥሮ የነበረም ሲሆን በአዲስ አበባ ተጨማሪ ምርምራ ካደረገ በኋላ በጉልበቱ የውጪኛው ክፍል ላይ የአጥንት ጉዳት ማስተናገዱ ተረጋግጧል።
ይህንንም ተከትሎ የአዞዎቹ እጅግ ወሳኝ ተጫዋች የሆነው አህመድ ለአንድ ወር ያህል ከሜዳ እንደሚርቅ እርግጥ ሆኗል።
- ማሰታውቂያ -
አህመድ ሁሴን በውድድር ዘመኑ 14 የሊግ ጨዋታዎች ላይ ለ1,191 ደቂቃዎችን የተጫወተ ሲሆን 7 ግቦችን በማስቆጠርም የሊጉን ኮከብ ግብ አግቢነት ከአንተነህ ተፈራ እና ያሬድ ብርሀኑ ጋር በጥምር እየመራ ይገኛል።


