መነሻ ገጽ አፍሪካ ከአፍሪካ 10 ታላላቅ ስታዲየሞች አንዱ የሆነው የኮት ዲቯር ስታዲየም ዛሬ ተመረቀ
አፍሪካዜናዎች

ከአፍሪካ 10 ታላላቅ ስታዲየሞች አንዱ የሆነው የኮት ዲቯር ስታዲየም ዛሬ ተመረቀ

አጋራ
አጋራ

“እንዳሰብኩት ለሃገሬ ኮት ዲቯር ኩራት የሆነው የኤቢምፔ ኦሊምፒክ ስታዲየም የምረቃ በዓል ላይ በጊዜ መድረስ ባለመቻሌ እጅግ በጣም አዝኛለው፡፡ የኤቢምፔ ኦሊምፒክ ስታዲየም ለአፍሪካና ለኮት ዲቯር ስፖርት ትልቅ ጌጥ ነው በዝግጅቱ ለምትሳተፉ ሁሉ መልካም የምረቃ በዓል ይሁንላችሁ::”ሲል መልዕክቱን ያስተላለፈው የቀድሞው የቼልሲና ተጫዋች ዲዲዬ ድሮግባ ነው፡፡

የኤቢምፔ ኦሊምፒክ ስታዲየም ዛሬ የሃገሪቱ ፕሬዚዳንት አላሳን ዋታራ በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተመርቋል፡፡ ጥቅምት 2016 ተጀምሮ ከአራት ዓመታት ሥራ በኋላ ዛሬ ምረቃውን ያደረገው ይሄ ግዙፍ ስታዲየም በቻይናና በኮት ዲቯር መንግስታት ትብብር የተሰራ ነው፡፡ ስታዲየሙ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ 143 ቢሊዮን የምዕራብ አፍሪካ ፍራንክ የፈጀ ሲሆን 60012 ሰዎችን የማስተናገድ አቅም እንዳለው ተጠቅሷል፡፡

“ይህን በሥነ-ህንጻ ውበቱ የአፍሪካ ጌጥ የሆነ፣ በቻይናና በኮት ዲቯር መንግስታት ትብብር የተሰራ ታላቅ ስታዲየም ከፊታችሁ ሆኜ ስመርቅ የሚሰማኝን ደስታ ቃላት ሊገልጹልኝ አይችሉም”ብለዋል፡፡

ይህ ስታዲየም በትልቅነቱ የካሜሮኑን ኦሊምቤ ስታዲየምና የዳካሩን ሊኦፖል ሴዳር ሴንጎር ስታዲየምን ተከትሎ ከአፍሪካ አስረኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ስታዲየም ሲሆን በመጪው መጋቢት ወር ኮት ዲቯር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የምታስተናግድበት ስታዲየም እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...