መነሻ ገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ የአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ እና ኮንፌዴሬሽን ካፕ የቅደመ ማጣሪያ ጨዋታዎች የተጫዋቾች ምዝገባ በዛሬው ዕለት ይጠናቀቃል
ቅዱስ ጊዮርጊስባህርዳር ከተማአፍሪካአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግካፍኮንፌድሬሽን ካፕ

የአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ እና ኮንፌዴሬሽን ካፕ የቅደመ ማጣሪያ ጨዋታዎች የተጫዋቾች ምዝገባ በዛሬው ዕለት ይጠናቀቃል

አጋራ
አጋራ

በአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ እና ኮንፌዴሬሽን ካፕ ተሳታፊ የሆኑ ክለቦች በቅደመ ማጣሪያ ጨዋታዎች የሚጠቀሙትን የቡድን ስብስብ ማስመዝገቢያ ቀነ ገደብ በዛሬው ዕለት ይጠናቀቃል ።

የውድድሮቹ የበላይ አካል የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን(CAF) በቅድመ ማጣሪያ የደርሶ መልስ ጨዋታዎች ላይ ክለቦች የሚጠቀሟቸውን ተጫዋቾች እንዲያስመዘግቡ ከሰኔ 24 ጀምሮ ክፍት አድርጎ ቆይታል ።

ለአንድ ወር የቆየው የተጫዋቾች ማስመዝገቢያ ጊዜም ዛሬ ለሊት 6:00 ላይ ያበቃል ።

ክለቦችም በደርሶ መልስ ጨዋታዎቹ የሚጠቀሟቸውን እና ዝውውር ፈፅመው ዝውውራቸው በየፌዴሬሽናቸው የፀደቁ ተጫዋቾችን እስከተጠቀሰው ሰዓት ድረስ የማስመዝገብ ግዴታ አለባቸው ።

በዛሬው ዕለት ልምምዳቸውን የሚጀምሩት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ባህርዳር ከተማም ከዛሬ ዝውውሮቻቸው መጠናቀቅ በኋላ አጠቃላይ ስብስባቸውን እንደሚያስመዘግቡ ይጠበቃል ።

እስከዛሬው ዕለት ድረስ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ባረጋገጣቸው ዝውውሮች መሰረት ቅዱስ ጊዮርጊስ የአስር ተጫዋቾቹን ውል ሲያራዝም አማኑኤል አረቦን ከለገጣፎ ለገዳዲ እንዲሁም ፋሲል ገብረሚካኤልን ከባህርዳር ከተማ አስፈርሟል ።

ባህርዳር ከተማ በበኩሉ ፍሬው ሰለሞንን ከሲዳማ ቡና ፣ አላዛር ማርቆስ ከሀዋሳ ከተማ ፣ ረጂብ ሚፍታህ ከቤንች ማጂ እንዲሁሕ ፍሬዘር ካሳን ከሀድያ ሆሳዕና ማስፈረሙ ይታወሳል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ፈረሰኞቹ ተጨማሪ ሁለት ተጫዋቾችን የግላቸው አደረጉ

ፈረሰኞቹ የሁለት ተጨማሪ ተጫዋቾችን ዝውውር አጠናቀቁ። በአሁኑ ሰዓት በሸራተን ሆቴል መግለጫ እየሰጡ...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ቅዱስ ጊዮርጊስ አራት ተጫዋቾችን የስብስቡ አካል ሲያደርግ የአማካዩ መፈረም አጠራጥሯል

በሰርቪያዊው አሰልጣኝ ጥቆማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ዝውውር ገብቷል። በቀጣዩ የውድድር ዘመን ሰርቪያዊውን...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሰርቪያዊው ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ መጥተዋል

ከፈረሰኞቹ ጋር አምስት የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ ያነሱት ሰርቪያዊው አሰልጣኝ ወደ ቀድሞው ክለባቸው...