By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የሊጉ መሪ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር አቻ ሲለያይ ፤ ሀምበሪቾ ዱራሜም ባደገበት አመት ከሊጉ የወረደበትን ዉጤት አስመዝግቧል !!
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የዲሲፕሊን ውሳኔዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስኢትዮጵያ ንግድ ባንክሀምበሪቾ ድራሜየጨዋታ ዘገባየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወላይታ ድቻ

የሊጉ መሪ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር አቻ ሲለያይ ፤ ሀምበሪቾ ዱራሜም ባደገበት አመት ከሊጉ የወረደበትን ዉጤት አስመዝግቧል !!

Ermias Misganaw
Ermias Misganaw 2 years ago
Share
SHARE

በሀያ ስምንተኛዉ ሳምንት የሊጉ መርሐግብር የመዝጊያ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር አንድ አቻ ተለያይተዋል።

ገና በጊዜ በኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች ተደጋጋሚ የግብ ሙከራዎች በጀመረዉ ጨዋታ ሁለቱም ክለቦች መጠነኛ ፉክክር ያስመለከቱን ሲሆን ፈረሰኞቹም ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ መጨዋታቸዉን ከቀጠሉ በኋላ በ21ኛዉ ደቂቃ ላይ የባንክ ተከላካዮች በሰሩት ስህተት የተገኘዉን ኳስ  ዳግማዊ አርአያ ተቆጣጥሮ ወደ ግብ ክልሉ ሲቀንሰዉ ተከላካዩ ኤፍሬም በራሱ ግብ ላይ አስቆጥሮ ፈረሰኞቹ መሪ መሆን ችለዋል።

ከግቧ መቆጠር በኋላ በሁለቱም ክለቦች በኩል ጎሎችን ለማስቆጠር የጋለ የሜዳ ላይ ፉክክርን እየተመለከተን የቀጠልን ሲሆን በዚህም ባንኮች አየቻነት ግብ ፍለጋ በተደጋጋሚ የፈረሰኞቹን የግብ ክልል ሲያንኳኩ የቆዩበት ሂደት ፍሬ አፍርቶ በ41ኛዉ ደቂቃ ላይ አቻ መሆን ችለዋል። በዚህም ከማዕዘን የተሻማዉን ኳስ ሳይመን ፒተር ሲገጨዉ በቅርብ ርቀት የነበረዉ ባሲሩ ዑመር ኳሷን ጨርፎ ወደ ግብነት በመቀየር በአጋማሹ መገባደጃ ወቅት አቻ ማድረግ ችሏል።

ከዕረፍት መልስ ሁለቱም ክለቦች በተሻለ የማጥቃት መነሳሳት በተደጋጋሚ ወደ ተቃራኒ ቡድን የግብ ክልል ለመድረስ ያደርጉ የነበረዉ ጥረት ጥሩ የሚባል የነበረ ቢሆንም ነገር ግን አፈፃፀም ላይ ሁለቱም ክለቦች ደካማ ሁነዉ ተስተዉለዋል። ደቂቃዎች እየገፉ በሄዱ ቁጥር ግን በመጠኑም ቢሆን እየተቀዛቀዘ በቀጠለዉ ጨዋታ በ76ተኛዉ ደቂቃ ላይ ፈረሰኞቹ በረመዳን የሱፍ አማካኝነት ግብ ማስቆጠር ችለዉ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ከጨዋታ ዉጭ በሚል ተሽሮባቸዋል።

- ማሰታውቂያ -

ከሁለት ደቂቃዎች በኋላ ሳይመን ፒተርን በቀይ ካርድ ያጡት እና ቀሪ ደቂቃዎችን በጎዶሎ ተጫዋች ለመጫወት የተገደዱት ባንኮች ምንም እንኳን በቀሪ ደቂቃዎች እጅጉኑ ጫና ፈጥረዉ መጫወት ቢችሉም ነገር ግን በጨዋታዉ ተጨማሪ ግብ ሳይቆጠር መርሐግብሩ አንድ አቻ በሆነ ዉጤት ፍፃሜዉን አግኝቷል።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ሀምበሪቾ ዱራሜ እና ወላይታ ዲቻ ጨዋታቸዉን ያለ ግብ በአቻ ዉጤት ፈፅመዋል።

አመሻሽ 12:00 ሰዓት ሲል በጀመረዉ የሁለቱ ክለቦች ተጠባቂ ጨዋታ ወላይታ ዲቻዎች በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች የተሻለ ብልጫ ወስደዉ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ዕድሎችን በመፍጠር እና የፈጠሯቸዉን ዕድሎች ወደ ግብነት በመቀየር ረገድ ግድ ደካማ ሁነዉ ተስተዉሏል። በተቃራኒው በይበልጥ ወደ መከላከሉ አመዝነዉ በመጫወት እንቅስቃሴያቸውን የቀጠሉት ሀምበሪቾዎች ደግሞ አልፎ አልፎ በሚያገኟቸዉ የመልሶ ማጥቃት እና የቆሙ ኳስ አደጋዎችን ለመፍጠር ሲጥሩ ተስተውሏል።

በዚህ ሂደት የቀጠለዉ የሁለቱ ክለቦች የመጀመሪያ አጋማሽ ጨዋታ ያን ያህል የጠራ የግብ ሙከራ ሳያስመለክተን ፍፃሜዉን ሲያገኝ ከዕረፍት መልስ በተሻለ ለማጥቃት በሚል ቢኒያም ፍቅሬን ቀይረዉ ወደ ሜዳ ያስገቡት ዲቻዎች በተደጋጋሚ የሀምበሪቾን የግብ ክልል በመፈትሹም ነገር ግን በሀምበሪቾዉ የግብ ዘብ ምንታምር መለሰ ጥሩ ብቃት ኳሶቹ ግብ ከመሆን ከሽፈዋል። ከዕረፍት መልስም እንደ መጀመሪያዉ አጋማሽ ሁለለ በጥብቅ መከላከል መጫወት የቀጠሉት ሀምበሪቾዎች በ52ተኛዉ ደቂቃ ላይ በተመስገን አማካኝነት ከርቀት ድንቅ ሙከራ ቢያደርጉም የግብ ዘቡ ቢኒያም ገነቱ አምክኖባቸዋል።

በዚህ ሂደት በቀጠለዉ ጨዋታ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ ዲቻዎች የተሻለ ብልጫን ወስደዉ በቢኒያም ፍቅሬ እና ናታን ጋሻዉ በመሳሰሉ ተጫዋቾቻቸው ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ማድረግ ቢችሉም ግብ ማስቆጠር ሳይችሉ ቀርተዉ ጨዋታዉ ያለ ግብ 0ለ0 በሆነ ዉጤት ተጠናቋል።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Ermias Misganaw
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ኢትዮጵያ ቡና በድል ጉዞዉ ሲቀጥል ፤ መቻልም ሲዳማ ቡናን በሰፊ የግብ ልዩነት ማሸነፍ ችሏል !!
Next Article የ2016 ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀያ ስምንተኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔ! እና 29ኛ ሳምንት የፕሮግራም ለውጥ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎችዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስ

ቡአይ ኩዌት ወደ ፈረሰኞቹ ቤት ለማምራት ተስማማ !

fitsum Wadu By fitsum Wadu 7 months ago
“አሸንፈን እንደምናልፍ በጣም እርግጠኞች ነን” ሎዛ አበራ “ተጋጣሚያችን ከኛ የተሻለ ምንም ነገር የለውም” አሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ
ሲዳማ ቡና የተጫዋቾቻቸውን ውል በማራዘሙ ተጠምደዋል !
Surafel Dagnachew wins best player of the year award
በኘሪሜየር ሊጉ  ሲዳማ ቡና መሪነቱን እሚያጠብበት እድል ሲያመክን :መከላከያ ድል ቀንቶታል !!!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?