ዛሬ ረፋድ 4 :00 ሰዓት ላይ በተደረገዉ ጨዋታ የኢትዮጵያ ከ 23 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የኢትዮጵያ መድህንን በመድህን ሜዳ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል ።
አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ሁለት የጨዋታ አሰላለፍ ይዘው በገቡበት ጨዋታ ዊሊያም ሰለሞን እና መስፍን ታፈሰ ሁለቱን የማሸነፊያ ግቦች ማስቆጠር ችለዋል። በኢትዮጵያ መድህን በኩል ከሽንፈት ያልታደገቻቸዉን ብቸኛ ግብ ተከላካዩ ፀጋሰው ድማሙ በራሱ ላይ አስቆጥሯል ።
የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ሀምሌ 10 ለሚጀምረዉ የሴካፋ ቻሌንጅ ካፕ ዉድድር በቀጣዮቹ ቀናት ዉስጥ ዉድድሩን ወደ ምታዘጋጀዉ ባህርዳር ከተማ የሚያመራ ይሆናል።
አስተያየት ይስጡ