በባህርዳር ከተማ አሰልጣኝነቱ በሰራው ጠንካራ ቡድን ያለውን አቅም ያሳየው አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ቀጣዩ የአዳማ ከተማ አሰልጣኝ ለመሆን ከጫፍ ደርሷል።
በፕሪሚየር ሊጉ እንዲቆዩ ያደረገው አሰልጣኝ ዘርአይ ሙሉ ወደ ሀዋሳ ከተማ በማቅናቱ ፊታቸውን ወደ አዲስ አሰልጣኝ ቅጥር ያዞሩት አዳማዎች አራት አሰልጣኞችን ካወዳደሩ በኋላ ዛሬ ከቀትር በኋላ ባደረጉት ስብሰባ አስልጣኝ ፋሲል ተካልኝን መምረጣቸው ታውቋል።
የክለቡ አመራሮች በቀጣይ ቀናቶች ከአሰልጣኙ ጋር ድርድር በማድረግ ሹመቱን ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።


