የዝዉዉር ገበያዉን በይፋ ከተቀላቀሉ በኋላ የተለያዩ ተጫዋቾችን ወደ ክለባቸዉ በመቀላቀል ላይ የሚገኙት ባህር ዳር ከተማዎች አመሻሽ ላይ ሶስተኛ ተጫዋች ከሰበታ ከተማ ማስፈረም ችለዋል።
አስቀድመው ሁለገቡን ተጫዋቾች ተመሰገን ደረሰን ከጅማ አባጅፋር እና ወጣቱን መሳይ አገኘሁ ከወላይታ ድቻ ወደ ቡድናቸዉ የቀላቀሉት ባህርዳሮች አሁን ደግሞ ሌላኛውን ወጣት ተጫዋች ፋአድ ፈረጃ ከሰበታ ከተማ ማስፈረማቸዉ ተረጋግጧል።
ከአዳማ ከተማ ታዳጊዎች ቡድን የተገኘው እና በዘንድሮዉ የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ ከክለቡ ከሰበታ ከተማ ጋር ጥሩ የሚባል አመትን ማሳለፍ የቻለዉ ፋአድ አሰልጣኝ አብርሐም መብራቱን ተከትሎ ከሰበታ ከተማ የጣናው ሞገድን የተቀላቀለ ሶስተኛዉ ተጫዋቾች መሆኑ ታዉቋል።


