መነሻ ገጽ አዳማ ከተማ አዳማ ከተማ እና አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ተለያዩ
አዳማ ከተማዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

አዳማ ከተማ እና አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ተለያዩ

አጋራ
አጋራ

አዳማ ከተማ ባደረገው ስብሰባ ዋና አሰልጣኙን ከክለቡ አሰናብቷል።

በክረምቱ የዝውውር መስኮት በርከት ያሉ ዝውውሮችን ፈፅመው ወደ ውድድር ቢገቡም ከተጠበቀው በታች በፕሪምየር ሊጉ ላይ ውጤት ማምጣት የቻሉት አዳማ ከተማዎች በ33 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ ካስቀመጡት አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ጋር ተለያይቷል።

የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ አዲስ አበባ ከተማ ፣ ሰበታ ከተማ ፣ መቻል ፣ ፋሲል ከነማ እና ሲዳማ ቡና ፣ በየመን ሊግ እንዲሁም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጭምር በአሰልጣኝነት ያገለገሉት አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ከውጤት መጥፋት ባሻገር በቡድኑ ውስጥ የሚገኙ አንዳንድ ተጫዋቾች በአሰልጣኙ ደስተኛ ያለ መሆናቸው ተደማምሮ በመጨረሻም የክለቡ ቦርድ ካደረገው ግምገማ በኋላ አሰልጣኙን አሰናብቷል።

በምትኩም ረዳቶቹ አሰልጣኝ ዳዊት ታደለ እና ዳዊት ሀብታሙ በቀጣዮቹ አራት ጨዋታዎች የሚያሳዩት ውጤት እየታየ ቡድኑን እንዲመሩ በቦታው ጊዜያዊ ሆነው በትግግዝ እንዲያገለግሉ ተሹመዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ሲዳማ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሲዳማ ቡና ቡድን መሪ ታገደ

በዮሴፍ ከፈለኝ የፕሪምየር ሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና የቡድን መሪው የቀድሞው ዳኛ ዕግድ...

ዜናዎችየዲሲፕሊን ውሳኔዎች

27ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አብዱላጢፍ ባምባ (መቐለ 70 እንደርታ) : ክለቡ ከ ወልዋሎ አዲግራት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...