ሞዓም አናብስቱ ከመስመር አጥቂው ጋር የመለያየታቸው ነገር የሰፋ መስሏል።
መቐለ 70 እንደርታ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ካስፈረማቸው ተጫዋቾች መካከል ፈጣኑ የመስመር አጥቂ ኪቲካ ጅማ ይጠቀሳል። ክለቡን በቋሚነት ከሚያገለግሉት መካከል አንዱ የሆነው የቀድሞው የገላን ከተማ ፣ ኢትዮጵያ መድን እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጫዋች ለመቐለ የአንድ አመት ውል ፈርሞ በክለቡ ላለፉት ስድስት ወራቶች መቆየት የቻለ ቢሆንም ክለቡ የአራት ወራት ደመወዙን መክፈል አልቻለም።
ይህንንም ጉዳይ በተደጋጋሚ ለክለቡ ቢያቀርብም ሰሚ ያጣው ተጫዋቹ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን በደብዳቤ አሳውቆ ክለቡ ከትላንት በስቲያ የካቲት 19/2018 አፋጣኝ ምላሽን ፌድሬሽኑ ይስጠኝ ቢልም የክለቡ አመራሮች ጉዳዩን ችላ በማለት ፌድሬሽኑ የጠየቀውን ቀናት በማለፋቸው ተጫዋቹ ለሁለት ወር አንድ ክለብ ለአንድ ተጫዋች ደመወዝ ካልከፈለ ይለያይ በሚለው ህግ መሠረት ተጫዋቹ እና ክለቡ ያላቸው እህል ውሀ ሊያበቃ መቃረቡን የተገኘሁ መረጃ አመላክቷል።


