ወልዋሎዋሎአዲግራት ዩንቨርሲቲ በሜዳው እንዲጫወት ተወሰነ።
ሜዳየ ለመጫወቻ ብቁ ነው ሲል የወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርሲቲ ያስገባውን ቅሬታ ፌደሬሽኑ ምላሽ ሰጥቷል። በዚህም አብይ ኮሚቴው የ13ኛ ሳምንት ጨዋታ ማለትም ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርሲቲ እና ቅዱስ ጊዮርጊስን የሚያስተናግድበት ጨዋታ ቀደም ብሎ በተወሰነው መሰረት ትግራይ አለም አቀፍ ስታዲየም እንዲያደርግ ፌደሬሽኑ በላከው ደብዳቤ አሳውቋል። የሜዳ ለውጥ ማድረግ እንደሚቻል እና በቀጣይ ለሚደረገው መደበኛ ስብሰባ እንደሚቀርብ ደብዳቤው ያትታል። የፌደሬሽኑ ደብዳቤ በተጨማሪም ሜዳው አይደለም ለፕሪምየር ሊግ ኢንተርናሽናል ጨዋታ የማስተናገድ አቅም እንዳለው በአድናቆት ገልጿል።
ፌደሬሽኑ የላከው ደብዳቤ የሚከተለው ይመስላል 👇👇👇👇