የቀድሞ የካፍ ፅሀፊ የነበሩት አሚር ፋህሚ በካንሰር ህመም ሲሰቃዩ ከቆዩ በኋላ በ36 አመታቸው ዛሬ ሂወታቸው አልፋል።
ካፍን 2017-2019 በፅሀፊነት ያገለገሉት አሚር ፋህሚ በቀጣይ 2021 የሚደረገው የካፍ ፕሬዝደንት ምርጫ እንደሚወዳደር አሳውቆ እንደነበር አይዘነጋም። ፅሀፊው ከዚህ ቀደም በፊፋ ማስተር ኢን ማኔጅመንት፣ህግ፣ ሁማኒቲስ ስፖርት ሙሁር ሲሆኑ። በካፍ ከፍተኛ ልምድ ከነበራቸው ሰዎች በቀዳሚነት ተርታ የሚሰለፉ ነበሩ። ከካፍ ፅሀፊነት ባሻገር ቱርክ ላይ የተደረገውን የ2013 ወጣቶች አለም ዋንጫ የውድድሩ ጥቅላይ አስተባባሪ የነበሩ ሲሆን። ከ2011 እስከ 2014 የአፍሪካ ኔሽንስ ካፕ ቶርናመንት ጀነራል ዳይሬክተርም በመሆን አገልግለዋል።