መነሻ ገጽ ዜናዎች ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ያልገባ የውክልና ውል ተቀባይነት የለውም ተባለ
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ያልገባ የውክልና ውል ተቀባይነት የለውም ተባለ

አጋራ
አጋራ

ማንኛውም የተጨዋቾች ወኪል በስሩ ያሉት ተጨዋቾች ውል ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ገብቶ ካልፀደቀ በስተቀር ተቀባይነት የለውም ሲል የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡

ከፌዴሬሽኑ በተገኘ መረጃ ፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት ሳይመጡና ውሉ በህጋዊነት ሳይፀድቅ ተጨዋቾቹ የኛ ናቸው የሚለው ውዝግብ በተደጋጋሚ ማጋጠሙን ገልጾ ተጨዋቹ ከክለቡ ጋር ሲፈራረም የሚፀድቀው ፌዴሬሽን ጽ/ቤት በመምጣት እንደሆነ ሁሉ የሶስተኛው ወገን ውልም የሚፀድቀው ፌዴሬሽኑ ባለበት እንጂ አየር በአየር አይሰራም ብሏል፡፡ ከውል ጋርም ተያይዞ ውሉ የሚፀድቀው ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ፌዴሬሽን ጽ/ቤት በመምጣት ብቻ መሆኑን ተገንዝበው የሚመጠበቅባቸውን እንዲፈፅሙ ጠይቋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አንዳንድ ተጨዋቾች የውክልና ክፍያ ላለመፈፀም የሚሄዱበት መንገድ ጥያቄ አስነስቷል፡፡ ሀትሪክ ባገኘችው መረጃ መሰረት የሶሶተኛ ወገን ፍቃድ የሌላቸው ወኪሎች ጋር በመደራደር ክለብ ካገኙ በኋላ ሕጋዊ ፍቃድ ስለሌላቸው አንከፍልም የሚሉ ተጨዋቾች መኖራቸው እየተነገረ ነው፡፡ ብልጣብልጥነት ያለባቸው ተጨዋቾች ወኪሉ ከፌዴሬሽኑ ጋር ፍቃድ እንደሌለው የሚያውቁትን ወኪል አነጋግረው ክለብ ሲያገኙ ስልካቸውን ማጥፋትና ቃል የገቡትን ክፍያ አለመፈፀም እየተለመደ መጥቷል፡፡

ተጨዋቾችና ክለቦች ፍቃድ ከሌላቸው ወኪሎች ጋር ያላቸውን ግንኙነት ማቆም ወይም ከተጠቀሙ የሚገባውን ክፍያ ለወኪሎቹ መስጠት የግድ ይሆናል ይሄ የሞራል ጉዳይ ነው ሲሉም የእግር ኳስ የሕግ ሰዎች ይናገራሉ፡፡
የሶስተኛ ወገን ውል በሕግ አስገዳጅነት የሌለው በመሆኑ ተጨዋቾችና ክለቦች ፍቃድ ከሌላቸው ወኪሎች ጋር የመስራት እድል እንደፈጠረላቸው ሀትሪክ ያኘችው መረጃ ያስረዳል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...