መነሻ ገጽ ዜናዎች ፋሲል ከተማ ከወላይታድቻ ጋር ሰበታ ላይ በነበረው ጨዋታ የክስ ደብዳቤ ለፌዴሬሽኑ አስገብቷል
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግፋሲል ከተማ

ፋሲል ከተማ ከወላይታድቻ ጋር ሰበታ ላይ በነበረው ጨዋታ የክስ ደብዳቤ ለፌዴሬሽኑ አስገብቷል

አጋራ
አጋራ

ትናንት ሰበታ ላይ በ21ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ኘሪሚዬር ሊግ ወላይታ ዲቻ ከፋሲል ከተማ ባደረጉት ጨዋታ የጦና ንቦቹ በእዮብ አለማየሁ የሀትሪክ ግቦች 3-0 አፄዎቹን ማሸነፋቸው ይታወቃል፡፡

በመሆኑም ፋሲል ከተማዎች በትናንተናው ጨዋታ በወላይታ ድቻ በኩል ተሰለፎ የተጫወተው ተጨዋች ሙባረክ ሽኩር ከዚህ በፊት፡ከመከላከያ፡ሀዋሳ ከተማ፡ መቆለ ከተማ፡ከኢለክትሪክና አርባምንጭ ከተማ ጋር ክለቡ ባደረጋቸው ጨዋታዎች 5 ቢጫ ካርድ ሞልቶት የትናንትናው ጨዋታ ሊያልፈው የሚገባና በደንቡ መሰረት ለፌዴሬሽኑ የቅጣት ክፍያ ሳይከፍል በትናንትናው ጨዋታ ለክለቡ ግልጋሎት መስጠቱ ተገቢ አይደለም በሚል ዛሬ የፋሲል ከተማ እግር ኳስ ክለብ ለእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ክስ አስገብቷል፡፡

ክለቡ አያይዞም የትናንትናው ጨዋታ ከመጀመሩ አስቀድመን ተጨዋች ሙባረክ ሽኩር መሰለፉ ተገቢ አለመሆኑን ክስ አስመዝግበናል ብለዋል፡፡

በመሆኑም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ጉዳዩን አጣርቶ ተጨዋቹ 5 ቢጫ ካርድ እያለበት መሰለፉ እውነታ ከሆነ ውጤቱ በፎርፌ አፄዎቹ ሊያሸንፉ ይችላሉ፡፡በሌላ በኩል የፋሲል ከተማ ክስ እውነት ካልሆነ ያስያዙት ገንዘብ ለፌዴሬሽኑ ገቢ ይሆናል፡፡

የጉዳዩን ግብረ መልስ አጣርተን በዚሁ በገፃችን የምንዘግብ ይሆናል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...