መነሻ ገጽ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ቅድመ-ዕይታ | ሲዳማ ቡና ከ ወልዋሎ አዲግራት .ዮ
ሲዳማ ቡናወልዋሎዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ቅድመ-ዕይታ

የጨዋታ ቅድመ-ዕይታ | ሲዳማ ቡና ከ ወልዋሎ አዲግራት .ዮ

አጋራ
አጋራ

 

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በሳምንቱ አጋማሽ የሚደረጉ ሲሆን ሰባት ጨዋታዎች ዛሬ (ረቡዕ) 6 ጨዋታዎች ሲደረጉ ቀሪ አንድ ጨዋታ ደግሞ ሀሙስ የሚደረግ ይሆናል። በነገው(ሀሙስ) እለት ከሚደረጉት ጨዋታዎች መካከል ሲዳማ ቡና ከ ወልዋሎ ጋር የሚያደርጉትን ጨዋታ ለእናንተ እንዲስማማ አድርገን እንደሚከተለው ዳሰነዋል። መልካም ንባብ።

ጨዋታ: ሲዳማ ቡና ከ ወልዋሎ
የጨዋታ ቀን: ሀሙስ ጥር 21/2012
የጨዋታ ሰዓት: 9:00
የጨዋታ አርቢትር: ፌደራል አርቢትር ባህሩ ተካ
የጨዋታ ቦታ: ሀዋሳ አርቴፊሻል ስታዲየም 

በ10ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ወደ ጎንደር ተጉዘው በፋሲል ከነማ የተሸነፋት ሲዳማ ቡናዎች በዚህኛው ሳምንት ወልዋሎን በሀዋሳ ስታድየም ሚያስተናግዱ ይሆናል።

መሀል ሜዳ ላይ ከዳዊት ተፈራ መነሻቸውን አድርገው ወደ ሁለቱም መስመር በሚላኩ ኳሶች እድሎችን ሚፈጥሩት ሲዳማ ቡናዎች ነገም ተመሳሳይ አቀራረብ ሊኖራቸው እንደሚችል ይገመታል።በተለይ አዲስ ግደይ እና ሀብታሙ ገዛሀኝ ከመስመር እየተነሱ ሚያደርግዋቸው እንቅስቃሴዎች ሲዳማ ቡና ተደጋጋሚ እድሎችን እንዲፈጥሩ ያግዛቸዋል።ተከላካይ መስመር ላይ ክፍተቶች እየታዩባቸው ሚገኙት ሲዳማ ቡናዎች የተጋጣሚያቸው ፈጣን የአጥቂ መስመር ተጨዋቾች በግምት ስታስገባ ከኃላ ሚሰርዋቸውን ስህተቶች መቀነስ ግድ ሚላቸው ይሆናል።

ጥንቃቄ ላይ መሰረት ያደርገ መልሶ ማጥቃትን ምርጫጨው ሚያደርጉት ወልዋሎች ነገም በተመሳሳይ የኳስ ቁጥጥር ብልጫን ለሲዳማ ቡና ሰጥተው በመልሶ ማጥቃት እድሎችን ለመፍጠር ሊሞክሩ ይችላሉ።ተጨዋቾችን በተለያዩ ሚናዎች በማጫወት ሚታወቁት አሰልጣኝ ዮውሀንስ ሳህሌ ነገም በተመሳሳይ በአንዳንድ ቦታዎች
የተለየ ሚና ለተጨዋቾቻቸው ሊሰጡ እንደሚችሉ ይገመታል።ከመስመር በሚጣሉ ኳሶች እድሎችን ለመፍጠር ሚሞክሩት ወልዋሎዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ አጨዋወታቸው ተገማች እየሆነ መምጣቱ የቡድኑ ውጤት አንዳጀማመሩ አንዳይሆን አድርጎታል።

በዘርአይ ሙሉ ሚመሩት ሲዳማ ቡናዎች በሜዳቸው 4 ጨዋታዎችን አካሂደው በሁለቱ ሲያሸንፋ በሁለቱ ሽንፈት አስተናግደዋል።በአራቱ ጨዋታዎች ላይ 9 ግቦችን አስቆጥረው 6 ግቦችን አስተናግደዋል።

ቢጫ ለባሾቹ በበኩላቸው ከሜዳቸው ውጪ ካደረግዋቸው 4 ጨዋታዎች ሁለቱ ላይ ማሸነፍ ሲችሉ በመቐለ 70 እንደርታና ባህርዳር ተሸንፈዋል።ወልዋሎዎች ከሜዳቸው ወጥተው ባደረጉዋቸው 4 ጨዋታዎች ላይ ከመቐለው ጨዋታ በስተቀር ግብ ማስቆጠር ችለዋል።በአራቱ ጨዋታዎች 7 ግቦችን አስቆጥረው 4 ግቦችን አስተናግደዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...