ዛሬ ጠዋት የተሰበሰበው የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በህክምና ኮሚቴ አባልነታቸው ጠንካራ ስራ እንደሰሩ የሚነገርላቸው ዶ/ር አያሌውን ለፕሬዝዳንታዊ ዕጩ ተወዳዳሪ ሲቀሰቅሱ አገኘኋቸው በሚል ከኮሚቴው ማሰናበቱን ገልጾ በስራቸው የያዙትን ቢሮና ንብረት እንዲያስረክቡ አዟል።
ሰኞና ማክሰኞ በነበረው የአዳማው የስፖርታዊ ጨዋነት መድረክ ላይ ጥናታዊ ጽሑፍ ማቅረባቸውና ፌዴሬሽኑን መተቸታቸው የፌዴሬሽኑን ቁጣ መቀስቀሱ ምናልባትም ለዚህ ውሳኔ እንዳበቃቸው ይነገራል።
በዚህ የአመራሮቹ ውሳኔ ዙርያ የኮሚቴው ሰብሳቢና የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባሉ ዶ/ር ነስረዲን አብዱራሂም አለመገኘታቸው ቅሬታ እንዳይፈጥር ተሰግቷል።
በሌላ በኩል ስራ አስፈጻሚው ሶስት የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ አባላትንም ሰይሟል።ሶስቱ ባለሙያዎች ነገ የስራ መመርያ ከተሰጣቸው በኋላ የፊታችን ሰኞ ስራ ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
አስተያየት ይስጡ