By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ
Share
Notification Show More
Latest News
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ሀትሪክ ስፖርት አትሌቲክስዜናዎች

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ

kidus Yoftahe
kidus Yoftahe 6 years ago
Share
SHARE

• ፌዴሬሽኑ የብር 2,000,000.00 (ሁለት ሚሊዮን ብር) ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉም በበኩሏ የብር 400,000.00 (አራት መቶ ሺህ ብር) ድጋፍ አድርጋለች፤

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በወሰነው መሰረት ዛሬ መጋቢት 17/2012 ዓ. ም. በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ጽ/ቤትና በኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር በመገኘት ለህዳሴ ግድቡ ግንባታና ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ የሚውል የብር 2,000,000.00 (ሁለት ሚሊዮን ብር) ድጋፍ አድርጓል፡፡

በድጋፍ አሰጣጡ ወቅት በማስተባበሪያ ም/ቤቱ የተገኙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቀ/ም/ፕሬዝዳንት ክብርት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉና የፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቢልልኝ መቆያ ሲሆኑ ፕሬዝዳንቷ ክብርት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ባስተላለፈችው መልእክት ፌዴሬሽናችን 9ኛ አመቱን ሊደፍን ጥቂት ቀናት ብቻ የቀሩትን ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከመጀመሪያው ጀምሮ አትሌቶችንና የአትሌቲክሱን ቤተሰቦች በማስተባበር በቦንድ ግዢ፣ በስጦታ፣ ታላላቅ ሩጫዎችን በማስተባበር ከቲ-ሸርት ሽያጭና ከመሳሰሉት እንቅስቃሴዎች ከፍተኛ ገቢ በማስገባት ከመንግስት ጎን መሆኑን ሲያረጋግጥ እንደቆየ አመልክታለች፡፡

- ማሰታውቂያ -

አሁንም ፌዴሬሽኑ ግንባር ቀደም በመሆን ለህዳሴ ግድቡ ግንባታ መፋጠን ያግዝ ዘንድ፣ እንዲሁም ሌሎች አካላት በቡድንም ሆነ በግል የድርሻቸውን ይወጡ ዘንድ ይሄንን አርአያነት ያለው ተግባር ሲፈጽም በርካቶች ከጎናችን ይሰለፋሉ የሚል እምነት አለኝ፤ ካለች በኋላ ግድባችን አድዋችን በመሆኑ ድጋፋችን ቀጣይ ነው፤ ስትል አስረድታለች፡፡

ከዚህ ጋር በማያያዝ አቶ ቢልልኝ መቆያ የኢአፌ ጽ/ቤት ኃላፊ ባሰሙት ንግግር ፌዴሬሽኑ ከአሁን በፊት በብር 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ ብር) ቦንድ በመግዛት ቀዳሚ አጋርነቱን ያረጋገጠ ሲሆን ዛሬም ያው የቦንድ ግዢ በብር 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ ብር) እንዲቀጥል በስራ አስፈፃሚው መወሰኑንና ከዚህ ቀደም ፌዴሬሽኑ ከቲ-ሸርት ሺያጭ ብር 3,000,000.00 (ሶስት ሚሊዮን ብር) ለማስተባበሪያ ጽ/ቤቱ ገቢ ማድረጉን ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ከግንባታው ጋር በተያያዘ ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ በግሏ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) ድጋፍ አድረጋለች፡፡

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ም/ቤት ጽ/ቤት ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሮማን ገ/ሥላሴ በዚህ ወቅት ባስተላለፉት መልእክት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ምሳሌያዊ ተግባር በጣም አበረታች መሆኑን አስረድተው ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ የም/ቤቱ አባል ከመሆኗም በላይ የክብር አምባሳደር መሆኗን ጠቁመው በእሷ የሚመራው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከስፖርት ፌዴሬሽኖች፣ ተቋማትና ማህበራት ግንባር ቀደም በመሆን ለፈጸመው አኩሪ ተግባር ምስጋናዬ ከፍ ያለነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

አያይዘውም አትሌቶች፣ የአትሌቲክሱ ቤተሰቦች፣ የሁሉም የስፖርት ተቋማት ይሄንን ፋና ወጊ ተግባር በመከተል የሃገር ወዳድነታቸውን በተግባር እንዲያስመሰክሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በተያያዘ ሌላ መረጃ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአለም አቀፍ ደረጃ ወረርሺኝ ተብሎ የተፈረጀውና የወቅቱ ስጋት የሆነውን የኮሮና ቫይረስ በመከላከል ተግባር የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በወሰነው መሰረት የብር 1,000,000.00 (አንድ ሚሊዮን ብር) ድጋፍ ለኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር በዛሬው እለት አስረክቧል፡፡

ተቀ/ም/ፕሬዝዳንቷ ክብርት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ በኢፌዲሪ ጤና ሚኒስትር ዋና መ/ቤት በመገኘት ድጋፉን ለክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር አስረክባለች፡፡ ኮማንደር ደራርቱ ከርክክቡ በኋላ ባስተላለፈችው መልእክት ማንኛውም ኢትዮጵያን እወዳለሁ የሚል ዜጋ በዚህ የጭንቅ ወቅት ከመንግስትና ከህዝባችን ጎን በመቆም ይሄንን አስከፊ ወረርሺኝ በሚችለው ሁሉ አግዞ ሊከላከል ይገባዋል ስትል ገልፃለች፤ አያይዛም መዘናጋት እንኳንስ ለእኛ ታዳጊ አገር ቀርቶ ለበለጸጉትም አስከፊ ውጤት ማስከተሉን በሚዲያዎች የምነሰማው የእለት ተእለት መርዶ ነው፤ ብላለች፡፡

አክላም ኮማንድር አትሌት ደራርቱ ቱሉ እኔ በግሌ የኮሮና ቫይረስን ስርጭት ለመከላከል የብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) ለኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር ድጋፍ ማድረጌን ልገልጽ አወዳለሁ ካለች በኋላ ሁሉም አገር ወዳድ ዜጋ በዚህ ወቅት በጋራ እንዲረባረብና ወረርሺኙን እንድንመክት ያስፈልጋል፤ በማለት ጥሪዋን አስተላልፋለች፡፡

ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር በበኩላቸው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በዚህ ወሳኝ ሰዓት ከጎናችን በመሆን ላሳየው አብሮነት እጅግ አድርጌ አመሰግናለሁ፣ ፌዴሬሽኑ በማንኛውም ሁኔታ ከመንግስት ጎን በመሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ እንደሚገኝ ግልፅ ነው፤ ያሉት ዶ/ር ሊያ … ክብርት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ በግሏ ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) ያበረከተችው ድጋፍ አስደናቂ ከመሆኑም በላይ ፈር ቀዳጅና የሚመሰገን ተግባር እንደሆነ አመልክተው ድጋፉ ሁሉንም ዜጋ አሳታፊ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡

Via- #የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን

You Might Also Like

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By kidus Yoftahe
Follow:
Hatricksport website Editor
Previous Article “የጣና ሞገድ ደጋፊዎች የራሳቸው ቀለም ያላቸዉ ምርጥ ደጋፊዎች ናቸው ፤ {Yellow Wall} የሚል መጠሪያ ካላቸው የዶርቱሞንድ ደጋፊዎች ጋር ይመሳሰሉብኛል” አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ (ባህር ዳር ከነማ) ክፍል-1
Next Article የድሬዳዋ ከተማ ስፖርት ክለብ ስራ አስኪያጅ እና ምክትል አሰልጣኝ ሰየመ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዋልያዎቹየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንዜናዎች

ዋልያዎቹ ሴራሊዮንን በማሸነፍ ዳግም ወደ አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ፉክክር ተመልሰዋል።

Muluken Tesfaye By Muluken Tesfaye 7 years ago
የቀድሞ የሉሲዎቹ ተጨዋች ኢትዮ ኤሌትሪክ አሰልጣኝ ሆነች !
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የገንዘብ ድጋፍ አደርገ
” ካሜሩን በሚዘጋጀው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ሀገሬን ወክዬ መሳተፍ እፈልጋለሁ ” አለልኝ አዘነ /ባህርዳር ከተማ/
ጋቶች ፓኖም ለግብፁ ኤልዱና ፈረመ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?